በደራሲ ታደሰ ቦጋለ የተፃፈውና “አንድነት ውይይት አንድነት” የተሰኘው ታሪካዊ ልቦለድ መፅሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ።
በ1960ዎቹ መጨረሻ መፅሐፉ በዩኒቨርሲቲና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ተቃውሞ፣ ለጭቁን ህዝብ ሲሉ ቤተሰባቸውንና ህይወታቸውን አሳልፈው ስለሰጡ ታጋዮች፣ ስለ አላማ ፅናታቸው ይተርካል - በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመርኩዞ በአሰቃቂው ትግል የተዋደቁትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ታሪክ በልብ ወለድ መልክ የሚተርከው መፅሐፉ በ513 ገፆች ተቀንብቦ በ250 ብር ለገበያ ቀርቧል።