Monday, 24 May 2021 00:00

“Ethiopia Through my Eyes” የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን አርብ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በሰዓሊ መምህርና የፎቶግራፍ ባለሙያ ወንዶሰን በየነ የተነሱ በርካታ ፎቶዎች ከአማርኛ ግጥም ጋር የሚቀርቡበት “Ethiopia Through my Eyes” የተሰኘ የፎቶ ግራፍ ኤግዚቢሽን የፊታችን አርብ ግንቦት 20 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ ካዛንቺስ በሚገኘው ራዲሰን ብሉ ሆቴል ይከፈታል።
“ፎቶግራፎቼ ለኔ የጥበብ ተጋሪዎቼ ናቸው፣ በጥልቅ እይታ ያነሳኋቸው ፎቶዎች ስሜቴንና ዕይታዬን ይገልጡልኛል” የሚለው ሰዓሊ መምህርና ፎቶግራፈር ወንዶሰን በየነ፣ በዚህ ስሜት ያነሳቸው መልከአምድርን፣ የሰው መልክን፣ የኑሮ ዘይቤንና ባህልን የሚያሳዩ ፎቶዎች በኤግዚቢሽኑ ለዕይታ እንደሚቀርቡ ታውቋል። በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ሰዓሊያን የፎቶግራፍ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪያን እንደሚታደሙ የተገለጸ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ የአማርኛ ግጥሞች እንደሚካተቱና ኤግዚቢሽኑ እስከ ረቡዕ ግንቦት 25 ቀን ለእይታ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል።

Read 19488 times