ብራንድ አፍሪካ የተባለው ተቋም የ2021 የአፍሪካ እጅግ ተወዳጅና ተመራጭ የንግድ ምልክቶችን ዝርዝር ከሰሞኑ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ የአሜሪካው ናይኪ በአፍሪካ የአመቱ እጅግ ተወዳጅ ብራንድ ለመሆን ችሏል፡፡
የጀርመኑ የአልባሳትና ጫማዎች አምራች አዲዳስ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፣ የደቡብ ኮርያው ሳምሰንግ ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ተወዳጅ ብራንድ መሆኑን ብራንድ አፍሪካ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
በአመቱ በአፍሪካ እጅግ ተወዳጅ ብራንዶች ዝርዝር ውስጥ ከአራተኛ እስከ አስረኛ ደረጃን የያዙትም፣ የአሜሪካው ኮካ ኮላ፣ የአሜሪካው አፕል፣ የቻይናው ቴክኖ፣ የጀርመኑ ፑማ፣ የጣሊያኑ ጊቺ፣ የጃፓኑ ቶዮታ እና የስፔኑ ዛራ ናቸው፡፡
በአፍሪካ ተወዳጅ ከሆኑ አፍሪካዊ ብራንዶች መካከል ቀዳሚነቱን የያዘው ኤምቲኤን ሲሆን የናይጀሪያው ዳንጎቴ ይከተላል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ