Saturday, 29 May 2021 14:27

አቫታር ከፍተኛ ገቢ በማግኘት ቀዳሚው ፊልም ሆኗል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ቪዡዋል ካፒታሊስት ድረገጽ ባለፉት 30 አመታት በአለማችን ከፍተኛ ጥቅል ገቢ ያገኙ ዝነኛ ፊልሞችን ዝርዝር ከሰሞኑ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ አቫታር በ2.85 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
እ.ኤ.አ በ2009 ለእይታ የበቃውና በጄምስ ካሜሩን ዳይሬክተርነት የተሰራው አቫታር አጠቃላይ ወጪው 237 ሚሊዮን ዶላር እንደሆነ ያስታወሰው ድረገጹ፣ ፊልሙ ለእይታ ከበቃበት ጊዜ አንስቶ በድምሩ 2.85 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱንም ገልጧል፡፡
አቬንጀርስ ኢንድጌም በ2.79 ቢሊዮን ዶላር የሁለተኛነትን ደረጃ ሲይዝ፣ ሌላኛው ዘመን አይሽሬ ፊልም ታይታኒክ በ2.2 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ በሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ድረገጹ አመልክቷል።
ስታር ዎርስ - ዘ ፎርስ አዌክን በ2.06 ቢሊዮን ዶላር፣ አቬንጀስርስ - ኢንፊኒቲ ዎር በ2.04 ቢሊዮን ዶላር፣ ጁራሲክ ዎርልድ በ1.67 ቢሊዮን ዶላር፣ ዘ ላዮንኪንግ በ1.65 ቢሊዮን ዶላር፣ ዘ አቬንጀርስ በ1.518 ቢሊዮን ዶላር፣ ፊዩሪየስ በ1.515 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ፍሮዝን ቱ በ1.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውንም መረጃው ያሳያል፡፡
ባለፉት 30 አመታት ከፍተኛ ገቢ ካገኙ 50 ፊልሞች መካከል 26ቱ በዲዝኒ ስቱዲዮ የተሰሩ መሆናቸውን የጠቆመው ድረገጹ፣ ዩኒቨርሳል ስቱዲዮ እና ዋርነር ብሮስ በተመሳሳይ 8 ፊልሞች እንደሚከተሉም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1210 times