Saturday, 05 June 2021 12:47

የህንዱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ 62 አገራትን ማዳረሱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ኮሮና ለስራ አጥነት የዳረጋቸው 220 ሚ. ይደርሳሉ ተባለ

           ባለፈው ጥቅምት ወር ለመጀመሪያ ጊዜ በህንድ የተገኘውና ከሌሎች የኮሮና ቫይረስ ዝርያዎች ሁሉ በቀላሉ የመሰራጨት አቅም እንዳለው የተነገረለት “B.1.617’’ የተባለ ዝርያ፣ እስካሁን ድረስ 62 አገራትን ማዳረሱን የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ከሳምንታት በፊት በአለማቀፍ ደረጃ ልዩ ስጋት ፈጥሯል በማለት በአደገኝነት የፈረጀውና ከሰሞኑ ደግሞ ‹ዴልታ› ሲል አዲስ ስም የሰጠው ይህ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ፣ ወደ 62 የአለማችን አገራት መዛመቱን ባለፈው ረቡዕ ያስታወቀው የአለም የጤና ድርጅት፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በጃፓን የተገኘውና ‹ጋማ› የሚል ስያሜ የተሰጠው የቫይረሱ ዝርያ በበኩሉ ወደ 64 የአለማችን አገራት መዛመቱን አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ የኮሮና ቫይረስ ዜና ደግሞ፣ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ፣ እስከ ዘንድሮው የፈረንጆች አመት 2021 መጨረሻ፣ ለስራ አጥነት የሚዳርጋቸው ሰዎች ቁጥር 220 ሚሊዮን ያህል ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመትና ወረርሽኙ ለድህነት የዳረጋቸው ሰራተኞች ቁጥር ከ100 ሚሊዮን ማለፉን፣ የአለም የስራ ድርጅት ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል፡፡
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰቱን ተከትሎ፣ በከፍተኛ ሁኔታ የስራ ሰዓቶች መቀነሳቸውንና የስራ ዕድሎች መዘጋታቸውን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰራተኞች ገቢያቸው መቀነሱን፣ ከስራ መፈናቀላቸውንና ለድህነት መዳረጋቸውን አስረድቷል፡፡

Read 1742 times