Saturday, 05 June 2021 13:34

ዝክረ አብደላ እዝራ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ሰው በሀገር ይወለዳል ይባላል። ግን ደግሞሀገርን የሚወልዱ ሰዎች አሉ።አብደላ እዝራ ጥበብና ፍቅር የተቃቀፉበት ሀገር በውስጡ ተሸክሟል።አብሮም ኖሯል። የምናውቀው በተባ ብዕሩ፣በሰላ ሂሱ፣ስለ ጥበብ ሲል ሁሉንምበሚተው ኪናዊ ፍቅሩ ነው። የአንጋፋ ደራስያንን ሥራፈትኗል፤የረገበውን የሀገር ጥበብ ቆንጠጥ አድርጎ
በከፍታ አጉልቶ ለማሳየት። ጠቢባን የሚያደንቁ ውብዓረፍተ ነገሮችን ዘክሯል። እምቡጥ አበቦቹን ወጣትደራሲያንን በሚሳሳ እጁ ኮትኩቷል። ቸርነቱ በጥበብም
በቁስም ነው። አብደላ እዝራ ጭው ባለ በረሃ ውስጥ ዕድሜውን ሙሉ ለጥበብ ንጽህና እንደ ምንጭ የፈሰሰ ጅረት ነበር! በፈረሰው ቅጥር -----የቆመ የጥበብ ዘብ!!
አዲስ አድማስ ጋዜጣ
ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም የአብደላ ዕዝራ  የ5ኛ ሙት ዓመት መታሰቢያ



Read 1431 times