Print this page
Monday, 07 June 2021 00:00

በአለማችን የምግብ ዋጋ በ10 አመታት ከፍተኛውን ጭማሪ አሳይቷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

      ላለፉት 12 ተከታታይ ወራት ጭማሪ ሲያሳይ የቆየው አለማቀፉ የምግብ ዋጋ፤ በግንቦት ወር ባለፉት 10 አመታት ከታየው ሁሉ ከፍተኛ ነው የተባለውን የ40 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ተመድ አስታውቋል፡፡
የአለም የምግብ ድርጅት ከሰሞኑ ይፋ ያደረገውን አለማቀፍ ሪፖርት ጠቅሶ ብሉምበርግ እንደዘገበው፣ ባለፉት 12 ወራት በሁሉም የምግብ አይነቶች ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ የተመዘገበ ሲሆን፣ በአመቱ የታየው የምግብ ዋጋ ጭማሪ እ.ኤ.አ በ2008 እና 2011 የተከሰቱትንና ከ30 በላይ በሚሆኑ አገራት ህዝባዊ ተቃውሞዎችን የቀሰቀሱ የምግብ ዋጋ ጭማሪዎችን የሚያስታውስ ነው ተብሏል፡፡
ድርቅና የዝናብ እጥረት በተለያዩ የአለማችን አገራት በቆሎና ቡናን በመሳሰሉ ምርቶች አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጭማሪ ማስከተሉን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ የእንስሳት ተዋጽኦዎች እንዲሁም የአትክልቶችና የቅባት እህሎች ምርትም በአለማቀፍ ደረጃ ቅናሽ ማሳየቱንና ይህም ለዋጋ ጭማሪ ሰበብ መሆኑን አመልክቷል፡፡

Read 2678 times
Administrator

Latest from Administrator