‹ላካታ ሴንተር 2› የሚል ስያሜ የተሰጠውና በአለማችን በቁመቱ 2ኛውን ደረጃ ይይዛል የተባለው ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በሩስያዋ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ሊገነባ መሆኑን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
ተቀማጭነቱ በስኮትላንድ በሆነው ኬትሊ ኮሎክቲቭ የተባለ የስነህንጻ ኩባንያ ዲዛይን የተደረገው ይህ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ፤ ቁመቱ 703 ሜትር እንደሚሆን የጠቆመው ዘገባው፤ በአሁኑ ወቅት በቁመቱ 1ኛ ደረጃን የያዘው 828 ሜትር የሚረዝመው የዱባዩ ቡርጂ ከሊፋ መሆኑንም አክሎ ገልጧል፡፡
150 ወለሎች እንደሚኖሩት የተነገረለት ህንጻው፤ የመኖሪያ ቤቶችና የገበያ አዳራሽን ጨምሮ የተለያዩ የመዝናኛና የንግድ እንዲሁም የስነጥበብ ተቋማት እንደሚያካትት የጠቆመው ዘገባው፤ግንባታው እየተገባደደ እንደሚገኝም አክሎ አስረድቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ