Wednesday, 16 June 2021 00:00

የአፍሪካ አየር መንገዶች 10.21 ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸው ተነግሯል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የአፍሪካ አየር መንገዶች ከኮሮና ቫይረስ ቀውስ ጋር በተያያዘ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 በድምሩ የ10.21 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንዳጋጠማቸው የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማህበር ከሰሞኑ ባወጣው አመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
የአፍሪካ የአየር መንገዶች በ2020 የፈረንጆች አመት ያጓጓዟቸው መንገደኞች ቁጥር በ2019 ከነበረበት በ63.7 በመቶ ቅናሽ በማሳየት 34.7 ሚሊዮን መድረሱን የማህበሩ ሪፖርት የጠቆመ ሲሆን በአመቱ ከአፍሪካ አየር መንገዶች መካከል በአገር ውስጥ፣ በአህጉራዊና በአለማቀፍ በረራዎች በድምሩ በርካታ ቁጥር ያላቸውን መንገደኞች በማጓጓዝ ቀዳሚነቱን የያዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሲሆን፣ ኢጅፕትኤር፣ ሮያል ኤር ሞሮኮ፣ ሳፋሪና ኬንያን ኤርዌይስ ይከተላሉ፡፡
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት በበርካታ የአለማችን አገራት የጉዞ ክልከላዎችን በማድረጋቸውና የጉዞና እንቅስቃሴ ገደቦች በመጣላቸው ሳቢያ፣ የአለማችን ስድስቱ ግዙፍ አየር መንገዶች በአመቱ በድምሩ 110 ቢሊዮን ዶላር ያህል ኪሳራ እንዳጋጠማቸውም ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 2471 times