የሳዑዲ አረቢያ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ከኮሮና ስጋት ጋር በተያያዘ ለ1442ኛ ጊዜ በሚካሄደው የዘንድሮው የሐጅ ስርዓት ላይ መሳተፍ የሚችሉት በአገሪቱ የሚገኙ ዜጎችና በነዋሪነት የተመዘገቡ ሰዎች ብቻ መሆናቸውን ከሰሞኑ አስታውቋል፡፡
ሚኒስቴሩ በሳምንቱ መጀመሪያ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፣ በዘንድሮው ሐጅ ስነስርዓት ለመሳተፍ የሚችሉት 60 ሺህ ያህል ሰዎች ብቻ ሲሆኑ፣ ስር የሰደደ በሽታ የሌለባቸው፣ የኮሮና ክትባት የወሰዱ እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 65 አመት ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ