Sunday, 27 June 2021 16:50

የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ በራሪ መኪኖች ውድድር ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኤርስፒደር ኢኤክስኤ የሚል ስያሜ የተሰጠውና በአለማችን ታሪክ በአይነቱ የመጀመሪያው እንደሆነ የተነገረለት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ በራሪ መኪኖች እሽቅድድም ከወራት በኋላ በድምቀት እንደሚካሄድ ዩሮኒውስ ዘግቧል፡፡
ማቲው ፒርሰን በተባሉ ስራ ፈጣሪ ሃሳብ አመንጪነት አሉዳ ኤሮኖቲክስና ኤርስፒደር በተሰኙ እህትማማች ኩባንያዎች አዘጋጅነት ባለፈው የፈረንጆች አመት ሊካሄድ ታስቦ የነበረውና በኮሮና ወረርሽኝ ክስተት ሳቢያ ተራዝሞ በመጪዎቹ 6 ወራት ጊዜ ውስጥ ሊደረግ ቀን በተቆረጠለት በዚህ ውድድር ላይ፣ በሰዓት 200 ኪሎ ሜትር ፍጥነት የመጓዝ አቅም ያላቸው በራሪ መኪኖች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተነግሯል፡፡
በውድድሩ የሚካፈሉት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ መኪኖች አማካይ ክብደት 130 ኪሎ ግራም እንደሚደርስ የጠቆመው ዘገባው፣ በሪሞት ኮንትሮል አማካይነት ከመሬት ላይ ሆነው በሚቆጣጠሯቸው አሽከርካሪዎች አማካይነት እንደሚንቀሳቀሱም ገልጧል፡፡
ውድድሩ በ3 የተለያዩ ስፍራዎች እንደሚካሄድ እንጂ ቦታዎቹ የትኞቹ እንደሆኑ አዘጋጆቹ በግልጽ አለመናገራቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ የበራሪ መኪኖች የሙከራ በረራ ከቀናት በፊት በደቡባዊ አውስትራሊያ በሚገኝ በረሃ በስኬታማ ሁኔታ መከናወኑንና ውድድሩ እውቅና እንደተሰጠውም አክሎ ገልጧል፡፡






Read 1197 times