Sunday, 27 June 2021 17:10

የአቶ ክቡር ገና መልዕክት

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የኢዜማው  አቶ ክቡር ገና  ምርጫ ቦርድ ውጤት ሳይገልፅ ብልፅግናን “እንኳን ደስ አላችሁ! “ በማለት  ፅፈዋል ።ጠ/ሚር አብይንም  “የዚህ ምርጫ አሸናፊ “በማለት አሞግሰዋቸዋል።
ኢዜማ ምርጫ ካሸነፈ  የአዲስ አበባ ከንቲባ ይሆናሉ ተብለው የተጠበቁት የኢዜማው አቶ  ክቡር ገና ዛሬ በፌስቡካቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ይሄን ፅፈዋል;
“ ኢትዮጵያውያን አብይ አህመድን ጠ/ ሚ  እንዲሆኑላቸው ወስነዋል። ጠ/ ሚሩም በውጭም  በውስጥም ጠላቶች   ማስፈራሪያ ቢደርስባቸውም ምርጫ እንዲከናወን አድርገዋል።ለዚህም ምስጋና ይገባቸዋል።”
“ጠ/ ሚሩ  ኢትዮጵያን አንግብው ለህዝባቸው ተስፋን በመመገባቸው  በብዙ መራጮች ልብ ገብተዋል“
“እኛ ተቃዋሚ  ፖለቲካ  ፓርቲዎች የሚጠበቅብን ስራ አልሰራንም። ይሄን ለምን ሆነ?  ብለን እራሳችን መጠየቅ፣ መፈተሽ፣ መወያየትና ለቀጣይ ስራዎች መዘጋጀት አለብን። ወጣት ፖለቲከኞችን ማምጣት አለብን። አምስት አመት  በጣም ትንሽ ግዜ ናት!።”
“ግን ሀገሪቱን ለሚገዛት ፓርቲ ምክር አለኝ ።የሰፋውን  የኑሮ ልዩነቱን ማቀራረብ ፣ድህነትን መቀነስ፣ የጤና አገልግሎትን ማስፋት፣ ስራ አጥነት ላይ ብዙ መስራት፣ ፍትህ  ላይ መስራት፣ የተሻለ የንግድ ስርአትን ፈጥሮ ስራ ፈጣሪን እና  ገቢን  ማስፋት፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ማስፋት፣ አንድነት ማምጣት ......” በማለት  ፅፈዋል።

Read 2383 times