መፅሐፍ ለንባብ በቃ
በዘመነ ኢህአዴግ (ህወሃት) ዘመን በተለይም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ የነበረውን አስቸጋሪ ወቅት ከህዝብ ወገንተኝነት ይልቅ ለአንድ ፓርቲ ሲያገለግል ነበር ያለውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ይህንን ሲያስፈፅሙ የነበሩ ባለሙያዎችን የሚዘረዝረውና በዚህ ውጥረት ውስጥ ሆነው የሙያ ስነ-ምግባራቸውን በመጠበቅ በከባድ ፈተና ውስጥ የነበሩትን ታማኝ የኢትዮጵያ ልጆች ገድል የሚቃኘው “ከስክሪኑ ጀርባ” (ከኢቲቪ ጋዜጠኛው አንደበት) የተሰኘ አዲስ መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ በወቅቱ የደረሰውን አጠቃላይ ቀውስና ችግር ወደጎን በመተው ቴሌቪዥኑ ለመንግስት በማጎብደድ አገራዊ ሚናውን ባመወጣቱ ቁጭት አድሮበት ለታሪክ እንዲቀመጥ ሲል የኢቲቪ ጋዜጠኛው አለኝታ ኢዮኤል መፅሐፉን ለመጻፍ መነሳቱንና መታሰቢያቱም በኢትዮጵያ ብሮድካስንግ ኮርፖለሬሽን በታማኝነት ሲያገለግሉ ለነበሩ ተገፍተው፣ ተባረውም ሆነ በራሳቸው ጊዜ ከተቋሙ ለለቀቁ፣ በሀገርም ሆነ በውጪ ላሉና አሁንም በፅናት እያገለገሉ ላሉ ሰራተኞች መደረጉን ጋዜጠኛው በመግቢያቸው አስፍረዋል፡፡ “ግርሻው፣ “ካድሬያዊነትና የሙያ ውድቀት”፣ “ብሄራዊ ንቅዘት”፣ የ”አቶ መለሰ እረፍትና የኢህአዴግ የጭንቀት ጊዜ”፣ “ድህረ መለስ”እና “እንባና ሳቅ” በሚሉ ስድስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ179 ገጽ የተመጠነው መፅሐፉ ፣ በ120 ብር እና በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል