Sunday, 27 June 2021 18:46

“ከስክሪኑ ጀርባ”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

መፅሐፍ ለንባብ በቃ
በዘመነ ኢህአዴግ (ህወሃት) ዘመን በተለይም ከ1997 ዓ.ም ምርጫ በኋላ የነበረውን አስቸጋሪ ወቅት ከህዝብ ወገንተኝነት ይልቅ ለአንድ ፓርቲ ሲያገለግል ነበር ያለውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ይህንን ሲያስፈፅሙ የነበሩ ባለሙያዎችን የሚዘረዝረውና በዚህ ውጥረት ውስጥ ሆነው የሙያ ስነ-ምግባራቸውን በመጠበቅ በከባድ ፈተና ውስጥ የነበሩትን ታማኝ የኢትዮጵያ ልጆች ገድል የሚቃኘው “ከስክሪኑ ጀርባ” (ከኢቲቪ ጋዜጠኛው አንደበት) የተሰኘ አዲስ መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ በወቅቱ የደረሰውን አጠቃላይ ቀውስና ችግር ወደጎን በመተው ቴሌቪዥኑ ለመንግስት በማጎብደድ አገራዊ ሚናውን ባመወጣቱ ቁጭት አድሮበት ለታሪክ እንዲቀመጥ ሲል የኢቲቪ ጋዜጠኛው አለኝታ ኢዮኤል መፅሐፉን ለመጻፍ መነሳቱንና መታሰቢያቱም በኢትዮጵያ ብሮድካስንግ ኮርፖለሬሽን በታማኝነት ሲያገለግሉ ለነበሩ ተገፍተው፣ ተባረውም ሆነ በራሳቸው ጊዜ ከተቋሙ ለለቀቁ፣ በሀገርም ሆነ በውጪ ላሉና አሁንም በፅናት እያገለገሉ ላሉ ሰራተኞች መደረጉን ጋዜጠኛው በመግቢያቸው አስፍረዋል፡፡ “ግርሻው፣ “ካድሬያዊነትና የሙያ ውድቀት”፣ “ብሄራዊ ንቅዘት”፣ የ”አቶ መለሰ እረፍትና የኢህአዴግ የጭንቀት ጊዜ”፣ “ድህረ መለስ”እና “እንባና ሳቅ” በሚሉ ስድስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ179 ገጽ የተመጠነው መፅሐፉ ፣ በ120 ብር እና በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 9549 times