Print this page
Monday, 12 July 2021 00:00

29% የአለማችን የጉዞ መዳረሻዎች መዘጋታቸው ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በመላው አለም ከሚገኙ የጉዞ መዳረሻዎች መካከል 29 በመቶ ያህሉ ከኮሮና ስጋት ጋር በተያያዘ ለአለማቀፍ የቱሪዝም መንገደኞች ሙሉ ለሙሉ ዝግ እንደሆኑ መቀጠላቸውን የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት ከሰሞኑ ባወጣው ሪፖርት ማስታወቁ ተነግሯል፡፡
በአለማችን ከሚገኙ የጉዞ መዳረሻዎች መካከል 34 በመቶ ያህሉ በከፊል ዝግ መሆናቸውን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ 36 በመቶ የሚሆኑት ከኮሮና ቫይረስ ነጻ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ለማያቀርቡ መንገደኞች ዝግ መሆናቸውን፣ 42 በመቶ ያህሉ ደግሞ ቫይረሱ በስፋት ከተሰራጨባቸው የተወሰኑ አገራት ለሚመጡ ቱሪስቶች ዝግ መሆናቸውን አመልክቷል፡፡
ብዛት ያላቸው የጉዞ መዳረሻዎች ከተዘጉባቸው የአለማችን አገራት መካከል የእስያና የፓሲፊክ አገራት እንደሚጠቀሱ የገለጸው የድርጅቱ ሪፖርት፣ በእነዚህ አገራት 70 በመቶ ያህሉ መዳረሻዎች ሙሉ ለሙሉ ዝግ መሆናቸውንና በአውሮፓ 13 በመቶ፣ በአፍሪካ 19 በመቶ፣ በመካከለኛው ምስራቅ ደግሞ 31 በመቶ መዳረሻዎች ለመንገደኞች ዝግ መሆናቸውን አመልክቷል፡፡


Read 2542 times
Administrator

Latest from Administrator