Print this page
Saturday, 04 September 2021 13:33

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በፈረንጆች አዲስ ዓመት አገልግሎት መስጠት ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

    በኢትዮጵያ በቴሌው ዘርፍ 8.5 ቢሊዮን ዶላር ድረስ ፈሰስ የማድረግ ዕቅድ አለው

         ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቴሌኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ በመጪው የፈረንጆች ዓመት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ገለፀ። ኩባንያው በኢትዮጵያ በቴሌው ዘርፍ እስከ 8.5 ቢሊዮን ዶላር ፈሰስ  ለማድረግ ዕቅድ አለን ብሏል።
የኩባንያው ኃላፊዎች ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተገለጸው፤ ኩባንያው በኢትዮጵያ የቴሌኮሚኒኬሽን ዘርፍ ላይ ተሰማርቶ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ፍቃድ አግኝቷል። የኩባንያው ዋና ስራ አስኪጅ ፒተር ኔድግዋ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ ዕድገት እያላየች ያለች አገር በመሆኗ በዚህች አገር ውስጥ ስራ መጀመሩን ለእኛ ከፍተኛ ዕድል ነው ብለዋል። ኩባንያው በመጪው ፈረንጆች አዲስ ዓመት ወደ ስራ ሲገባ ዘመናዊ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎቶችን ተደራሽ እንደሚያደርግም ተጠቁሟል።

Read 13495 times
Administrator

Latest from Administrator