በያዝነው የፈረንጆች አመት 2021 ብቻ በአፍሪካ አህጉር ከ48 ሺህ በላይ ሰዎች የደረሱበት ሳይታወቅ ደብዛቸው ጠፍቶ መቅረታቸውንና ከእነዚህም ውስጥ ወደ 22 ሺህ የሚጠጉት ለአካለ መጠን ያልደረሱ ህጻናት መሆናቸውን አለማቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
አብዛኞቹ ሰዎች ጠፍተው የቀሩት ከእርስ በእርስ ግጭት፣ ብጥብጥ፣ የተፈጥሮ አደጋዎችና ስደት ጋር በተያያዘ መሆኑን የጠቆመው ኮሚቴው፣ ጠፍተው ከቀሩት 48 ሺህ ሰዎች መካከል 82 በመቶ የሚሆኑት ወይም 40 ሺህ ያህሉ በእርስበርስ ግጭት ውስጥ ከሚገኙ ሰባት የአፍሪካ አገራት የጠፉ መሆናቸውንም አመልክቷል፡፡
በአህጉሩ ከተመዘገበው አጠቃላይ የጠፉ ሰዎች ቁጥር ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ናይጀሪያውያን መሆናቸውንም ኮሚቴው አክሎ ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ