Saturday, 11 September 2021 00:00

ይህ የአዲስ ዓመት ስጦታ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ለኢትዮጵያ ወሳኟን ጎል በዚምባቡዌ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት ያስቆጠረው የዋልያዎቹ የመሃል ተከላካይ አስቻለው ታመነ ከጨዋታው በኋላ በሰጠው አስተያየት “በቅድሚያ መላውን የኢትዮጵያን ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እፈልጋለሁ። ይህ የአዲስ ዓመት ስጦታ ነው። ለረጅም ደቂቃ ጨዋታውን አቋርጠውት ነበር። ግብ ጠባቂውም የተለያየ ነገር ሲያደርግ ነበር ፤ ከባዕድ አምልኮ ጋር በተያያዘ። ሆኖም ፍፁም ቅጣት ምት በራስ የመተማመን ጉዳይ ነው። እኔም ያንን ብዙ ትኩረት አልሰጠሁትም። ከዚህ በፊት ፍፁም ቅጣት ምት ላይ ብዙ ችግር የለብኝም ፤ የእሱ ተግባርም ላይ ትኩረት አላደረኩኝም። በክለብም በብሔራዊ ቡድንም እመታ ስለነበር እና በእንደዚህ ዓይነት ነገር ስለማላምንበት የግብ ጠባቂው ተግባር አላደናገረኝም ፤ ምንም ውስጤን አልረበሸውም። በጥሩ ሁኔታም ላስቆጥር ችያለሁ።›› - ሶከር ኢትዮጵያ፡፡

Read 1289 times