በድግሪ መርሃ ግብር በአካውንቲንግና ፋይናንስ በደረጃ በቴክኒክና ሙያ የትምህርት ዘርፎች ደግሞ በማርኬቲንግ በአካውንቲንግና በሰው ሀይል አስተዳደር ሙሉ እውቅና አግኝቶ በማስተማር ላይ ሚገኘው ሳልሳዊ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካውንቲንግና በሰው ሀይል አስተዳደር በደረጃ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነሀሴ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በኦሮሞ ባህል ማዕከል አስመረቀ፡፡ በዕለቱም ከትምህርት ቢሮና ከሌሎችም ተቋማት የተጋበዘ የክብር እንግዶች በተገኙበት ተማሪዎቹን ያስመረቀው ሳልሳዊ ኮሌጅ ዲን አቶ ተስፋዬ ዳዲ ተማሪዎቹ በ2013 ዓ.ም በሀገር ላይ የተከሰተውን የሰላም መደፍረስና ኮቪድ -19ን ተቋቁመው በመመረቃቸው ተማሪዎቹም መምህራንም ሆኑ የተማሪ ቤተሰቦች ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል።
በኢትዮጵያ ብሄራዊ ኮሚሽን የዩኔስኮ ዋና ኮሚሽነር ቤዛዊት ግርማ (ዶ/ር) በክብር እንግድነት ተገኝተው ተማሪዎችን ከመረቁ በኋላ ወደ ስራው አለም ሲቀላቀሉ ስንቅ የሚሆናቸውን ቁልፍ መልዕክቶች ለተማሪዎቹ አስተላልፈዋል። በእለቱም እጩ ተመራቂዎች የተመራቂ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃ ስነ ስርቱ ታመው ነበር።
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና