Print this page
Friday, 01 October 2021 00:00

በትግራይ 14 በመቶ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው መመለስ እንደማይፈልጉ ተገለፀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በትግራይ በጦርነት ሳቢያ ከትውልድ ቀያቸው ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል 14 በመቶ ያህሉ ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው መመለስ እንደማይፈልጉ አለማቀፍ ተቋማት በሰራው ጥናት  አመልክቷል፡፡
የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ድጋፍ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ከትናት በስቲያ ይፋ ባደረገው የጥናት ሪፖርት፤ ከቀየአቸው በተፈናቀሉ ዜጎች ፍላጎት ላይ አተኩሮ በተሰራው ጥናት መሰረት 86 በመቶ የሚሆኑት በቀድሞ ቀዬአቸው ሠላም ከተረጋገጠና በቂ የምግብ አቅርቦት ካገኙ ለመመለስ እንደሚፈልጉ ቀሪዎቹ 11 በመቶ ተፈናቃዮች ግን ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው መመለስ እንደማይሹ ገልጸዋል፡፡
በትግራይ በጦርነቱ ሳቢያ ከተፈናቀሉ ዜጎች መካከል 95 በመቶ ያህሉ በአሁኑ ወቅት በእጅጉ የቸገራቸው የምግብ አቅርቦት እጥረት መሆኑን መግለፃቸውን የሚጠቁመው ሪፖርቱ በተጨባጭም ታጣቂዎች መንገድ በየጊዜው በመዘጋታቸው ምክንያት ለምግብ እጥረት ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ወደ ቀድሞ ቀያቸው መመለስ የሚፈልጉትን ለመመለስ እንዲሁም በሌላ አካባቢ ለመስፈር የሚፈልጉትን ማስፈር ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑም በሪፖርቱ ተካትቷል፡፡
በአጠቃላይ 20 ሺህ ያህል ሰዎችን ሊያሰፍር መቀሌ አካባቢ በሚገኝ ቦታ ላይ 2.727 ሰዎችን በቋሚነት ማስፈር መቻሉንም ተመልክቷል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊነት ጉዳዮች ሃላፊ ማርቲን ግሪ ፎዝ በትግራይ የከፋ ረሀብ ከመከሰቱ በፊት በሁሉም አቅጣጫ መንገዶች ክፍት ሆነው፣ ያልተቋረጠ የእርዳታ አቅርቦት እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Read 12260 times
Administrator

Latest from Administrator