Print this page
Friday, 01 October 2021 00:00

አዲሱ የአማራ ክልላዊ መንግስት ቅድሚያ ትኩረቱ የህልውና ዘመቻውን በፍጥነት ማጠናቀቅ እንደሚሆን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

አዲስ የተመሰረተው የአማራ ክልላዊ መንግስት የቅድሚያ ትኩረቱ ከፌደራል መንግስት ጋር በመሆን የህልውና ዘመቻውን በአጭር ጊዜ  በማጠናቀቅ፣ ዘላቂ ሠላም ማስፈን እንደሚሆን አስታውቋል፡፡
ክልሉን ላለፉት 15 ወራት በርዕሰ መስተዳደርነት ከመሩት አቶ አገኘሁ ተሻገር መንበረ ስልጣኑን የተረከቡት ዶ/ር ይልቃል ከፈለ ስለ መንግስታቸው የትኩረት አቅጣጫዎች ባደረጉት ንግግር፣ የመጀመሪያው ተግባር በትህነግ ወረራ በሃይል የተያዙትን የአማራ መሬቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ማስለቀቅ እንደሚሆን አብራርተዋል፡፡
የዚህ ዘመቻ ፍጻሜም “የጁንታውን” ሃይል  ሙሉ ለሙሉ የሚቀብር እንደሚሆን ይጠበቃል ብለዋል-ርዕሰ መስተዳደሩ፡፡
በጦርነቱ ወቅት የተፈናቀሉ መልሰው እንዲቋቋሙ የማድረግ ተግባር ከህልውና ዘመቻው ጎን ለጎን በትኩረት እንደሚሰራ የተናገሩት ለዚህም የክልሉ መንግስት የድጋፍ ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የአማራ ክልል በጦርነቱ መጎዳቱንና የልማት እንቅስቃሴዎች መስተጓጎላቸውን ተከትሎም ክልሉ ለ2014 ከመደበው የ80 ቢሊዮን ብር በጀት ውጭ የተጨማሪ በጀት ጥያቄ ለፌደራል መንግስቱ ማቅረቡ የተጠቆመ ሲሆን ተጨማሪው በጀት በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢዎች መልሶ ማቋቋሚያ ይሆናል ተብሏል፡፡
አዲሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር ይልቃል ከፈለ የክልሉን የአስር ዓመት መሪ እቅድ ለማሳካት መንግስታቸው በግብርና፣ በስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ላይ አተኩሮ ይሰራል ብለዋል፡፡
አዲሱ የአማራ አስተዳደር የተቃዋሚ ፓርቲ አብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጣሂር መሃመድን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ እንዲሁም የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ (አዲሀን) ሊቀ መንበር አቶ ተስፋሁን አለምነህን የክልሉ ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ሃላፊ አድርጎ የሾመ ሲሆን የተፊካካሪ         ፓርቲዎች አባላት በመንግስት ውስጥ የማሳተፍ ተግባር በየደረጃው ባሉ የመንግስ መዋቅሮችም ይቀጥላል ተብሏል፡፡

Read 12315 times
Administrator

Latest from Administrator