በመላው አፍሪካ የሚገኙ የጥበብ፣ የባህል፣ የቅርስና የቢዝነስ ሰዎች የሚሳተፉበት “አፍሪካ ሰለብሪቲስ” ልዩ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ለስምንት ቀናት ይካሄዳል፡፡የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን 2021 ዓ.ምህረትን የጥበብ፣የባህል፣ ቅርስና የቢዝነስ ዓመት አድርጎ በአጀንዳ 2063 ስር ማካተቱን ተከትሎ ይህ በርካታ ሁነቶች በአንድ ላይ የሚከወኑበት መርሃ ግብር መሰናዳቱን አዘጋጆቹ ረቡዕ ረፋድ ላይ በቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ አፍረካ ሰለብሪቲ ሁነት በሁሉም አፍሪካ አገራት የሚገኙ የቢዝነስ የመዝናኛ የባህልና ቅርስ እንዲሁም የቢዝነስ ሰዎች የሚሳተፉበት ሲሆን “ክለብ አዲስ” እና ሌጀንደሪ ጎልድ ሊሚትድ ናይጀሪያና ፕሪስቲን ማርኬቲንግ በጋራ እንዳዘጋጁት ተገልጿል፡፡ በሁነቱ ላይ ከተለያየ የአፍሪካ ሀገራት የሚመጡ ተሳታፊዎች የየሀገራቸውን ባህል፣ቅርስ፣የቱሪስት መስህቦች፣የቢዝነስ ስራዎችና የፋሽን ስራዎችን ለእይታ የሚቀርቡበት ነውም ተብሏል፡፡
Saturday, 09 October 2021 00:00
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና