Print this page
Saturday, 09 October 2021 00:00

የሃማ ቱማ ስብስብ ግጥሞች እየተሸጠ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በቀድሞው የኢህአፓ መሥራችና ደራሲ ሃማ ቱማ (እያሱ አለማየሁ) የተጻፉ የእንግሊዝኛ ግጥሞች በቤተማርያም ተሾመ  ወደ አማርኛ ተተርጉመው፣ "የሃማ ቱማ ስብስብ ግጥሞች" በሚል ርዕስ ታትሞ ለሽያጭ ቀረበ፡፡ በመጽሐፉ የእንግሊዝኛ ግጥሞችና ትርጉማቸው ጎን ለጎን መታተማቸው ታውቋል፡፡  
ሀማ ቱማ በእንግሊዘኛ ግጥሞቹ አለም አቀፍ ዕውቅናን የተቀዳጀ  ደራሲ ሲሆን በበርካታ የፖለቲካ ስላቅ  መጣጥፎቹም  ይታወቃል። ብዙዎች “የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ታሪክ” በሚለው ስራው ይበልጥ ያውቁታል።
በሙያው መካኒካል መሀንዲስ የሆነው ቤተማርያም፤ ከዚህ ቀደም  “ሦስተኛው ቤተመቅደስ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡ በቅርቡ ደግሞ “ጠያይም መላእክት" የተሰኘ አዲስ ስራውን ለንባብ እንደሚያበቃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ቤተማርያም በፌስ ቡክ ገፁ በሚያስነብባቸው ግጥሞቹም ይታወቃል።
የሃማ ቱማ ስብስብ ግጥሞች  በጃፋርና ሌሎች መጻህፍት መደብሮች እየተሸጠ ሲሆን መጽሐፉ  በቅርቡ በደማቅ ሥነስርዓት እንደሚመረቅም  ቤተማርያም ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ ከዚህ በታች ከመጽሐፉ የተወሰደ አንድ የእንግሊዝኛ ግጥም ከእነ ትርጉሙ ቀርቧል፡፡
 ***
Just a Nobody
The dead man was no one,
just a man in tattered clothes,
no shoes,
just a coin in his pocket,
no id cards, no bus ticket.
He was a nobody,
dirty and skinny,
a no one, a nobody
who clenched his hand before he died?
When they pried open his fingers
this nobody,
they found a whole country.
***
ማንም ምንምነት
ቡትቶ የለበሰ አካሉ የገረጣ፣
ጫማ የማያውቀው እግሩ መጅ ያወጣ።
ምንም ‘ማይታወቅ “እከሌ” ‘ማይባል፣
ከስቶና ታርዞ አንድ ምስኪን ሞቷል።
አባከና ሊለው ማንም የማይደፍር፣
ኪሱ አንዳች የሌለው ከድንቡሎ በቀር።
ከቁብ የማይፃፍ ማንም ያልነበረ፣
ከመሞቱ በፊት ጣቶቹን ቆልፎ ጨብጦ ነበረ።
እጆቹን ፈልቅቀው ሲፈታ ጭብጡ።
ከጣቶቹ መሀል ሀገሩን አገኙ ፣ሀገሩን አወጡ።



Read 1196 times
Administrator

Latest from Administrator