Saturday, 23 October 2021 13:55

እንኳን በዕውን በፊልም የማይታመን ድርጊት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ሰሞኑን በታላቋ አገር አሜሪካ፤ ፊላዴልፊያ ግዛት  ውስጥ  ተፈጸመ የተባለው  ጉዳይ ብዙዎችን ጉድ አሰኝቷል። እንኳን በገሃዱ ዓለም ቀርቶ በሆሊውድ ፊልሞችም ይቅርና በፊልምም ሆነ በልብወለድ ቢቀርብ የሚታመን አይደለም። ግን ድርጊቱ በእውን ተከስቷል- በአሜሪካ ምድር። ያውም በጠራራ ፀሃይ። ያውም በአደባባይ፤ ሰዎች በተሰበሰቡበት። አዎ ምድር ለምድር በሚምዘገዘግ ባቡር ውስጥ  ነገር ይጀምራታል-ይተነኩሳታል። ምድር ከፖሊስ እስከ ጋዜጠኛም ጉድ አሰኝቷል።
ድርጊቱ የተከሰተው ባለፈው ረቡዕ ነው። በፊላዴልፍያ ግዛት የምድር ለምድር የመንገደኞች ባቡር  ውስጥ 10  መንገደኞች ተሳፍረዋል።
ፌርማታ የተሳፈረው የ35 ዓመቱ ፊትሶን ንጎ የተባለ የጎዳና ተዳዳሪ ጎልማሳ ብቻዋን ተቀመጠች አንዲት ተሳፋሪ አጠገብ ሆዶ ይቀመጣል። ብዙም ሳይቆይ ከዚህች  ከማያውቃት ተሳፋሪ ጋር ትግል ይጀምራል። ደጋግማ  እየገፈተረች ራሷን ለመከላከል ብትሞክርም  በመጨረሻም ግን አልቻለችም ተሸነፈች።
ያ ሁሉ ተሳፋሪ ባለበት አስገድዶ ይደፍራታል። አሳፋሪውና አሳዛኙ ነገር አንድም ሰው ጣልቃ ገብቶ ከጥቃቱ ሊያድናትና ሊታደጋት አለመቻሉ ነው። ሌላው ቀርቶ ለፖሊስ እንኳን ለመደወል የሞከረ አልነበረም። ሁሉም ግን በሞባይል ካሜራ ጥቃቱን እየቀረፀ ነበር።
አንደኛው ፌርማታ ላይ ፖሊስ ደርሶ ጥቃት ፈፃሚውን በቁጥጥር ስር እስኪያውለው ድረስ ለ6 ደቂቃ ያህል ተሳፋሪዎቹ ድርጊቱን ሲቀርፁ እንደነበር ባቡሩ ውስጥ የተገጠመው የቅኝት ቪዲዮ ካሜራ ያረጋግጣል።
ተሳፋሪው ሴትየዋን ከጥቃቱ ለማዳን ግን መረዳቱ ቢቀር እንኳን ይሄን አሰቃቂ ጥቃት በፊልም  እየቀረጸ ከ5 ደቂቃ በላይ የማየት ብርታት እንዴት ኖረው  ፍላጎት አለማሳየቱ ከፍተኛ ጥናት የሚጠይቅ መሆኑ አያጠራጥርም።
“ባቡሩ ውስጥ ከነበረው ብዙ ተሳፋሪ አንጻር፣ ቢያንስ አንዳቸው ጣልቃ ገብተው አንድ የሆነ ነገር ማድረግ ነበረባቸው” ያለው አንድ የአካባቢው ፖሊስ፤ “እንዲህ ያለ ድርጊት ሲፈጸም ነው ዝም ብሎ ያያል፤ ህብረተሰባችን የደረሰበት ቀውስ ይናገራል፤ በጣም የሚረብሽ ነገር ነው” ብለዋል።
በነገራችን ላይ ፖሊስ በሴትየዋ ላይ ስለተፈፀመው ጥቃት  በሰጠው መግለጫ፤ “አስፈሪ የወንጀል ድርጊት ነው ብሎታል።
ማንም ሰው እንዲህ ያለ ድርጊት ሲገጥመው ወዲያውኑ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግም አስበዋል። “ድርጊቱን ሲመለከቱ የነበሩ ሰዎች አሉ። አንዱ ተሳፋሪ እንኳን 911 ቢደውል ኖሮ፣ ጥቃቱን በፍጥነት ማስቆም ይቻል ነበር” ነው ያሉት ፖሊሱ። ጥቃት ፈጻሚው አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ በ3 የወንጀል ድርጊቶች በፍ/ቤት ክስ እንደተመሰረተበት ታውቋል።
የጥቃቱ ተጎጂ ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል መወሰዷን የጠቆመው ፖሊስ፤ በርካታ መረጃዎች መስጠቷን በመጥቀስም “በጣም ጠኝካራ ሴት ናት” ሲል ብርታቷን አድንቋል።

Read 3619 times