Monday, 01 November 2021 06:08

ተማሪዎች ለአማፂው የፃፉት ደብዳቤ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ውድ ህወኃት፡-
ሰዎች ክፋትህን ለመግለፅ በሰይጣን ይመስሉህ ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ክፋቱ መጠን አጥቷል በሚል መግለጫ ቃላት አጥተው ሲቸገሩ ታዝቤአለሁ፡፡ አንተ ራስህን ይገልፀኛል ብለህ የምታስበው ቃል እንደሚኖርህ አልጠራጠርም፡፡
ካላስቸገርኩህ ብትነግረኝ ደስ ይለኛል፡፡ምስጢር እንደምጠብቅ ቃል እገባለሁ፡፡
ሳሚ፤ 7ኛ ክፍል
ውድ ህወኃት፡-
ህወኃት ከጥፋትና ውድመት በስተቀር የሚያውቀው አንዳችም በጎ ነገር የለም ሲባል እሰማለሁ፡፡
ይሄ ሃሰተኛ ውንጀላ መሆኑን በማስረጃ ልታሳምነኝ ትችላለህ፡፡ እኔ ለማመን ዝግጁ ነኝ፡፡ አደራ እሱንም ደሞ እንዳትዋሸኝ፡፡
 ገነት፤ 8ኛ ክፍል
ውድ ህወኃት፡-
ህዝብ መግደልና ማፈናቀል እንዲሁም ንብረትም ማውደም የሚበቃህ መቼ ነው?
“ሲኦል ስገባ ነው” እንዳትለኝና እንዳላዝንብህ፡፡ መልሱን በጉጉት እጠብቃለሁ፡፡
ጆሴፍ፤ 6ኛ ክፍል
ውድ ህወኃት፡-
አንዳንዶች ህወኃት ትናንሽ ህጻናትን ጦር ሜዳ ይልካል ብለው ሲያወሩ ሰምቼ አላመንኳቸውም፡፡
"የፈለገ ሰይጣን ብትሆን አታደርገውም” ብዬ አስባለሁ፡፡ ከአንተ ከራስህ ግን እውነቱን መስማት እፈልጋለሁ፡፡ እውነቱን ካልነገርከኝ ከት/ቤት ጓደኞቼ ጋር ሰልፍ ለመውጣት ተመካክረናል፡፡ እስከ መጪው እሁድ ብቻ ነው የምጠብቅህ፡፡  
ቢኒያም፤ 7ኛ ክፍል
ውድ ህወኃት፡-
“ህወኃት ት/ቤታችሁን አፍርሶታል” ተብለን እስካሁን ድረስ ትምህርት አልጀመርንም፡፡ ከክረምት ጀምሮ ቤት ውስጥ ተቀምጠን ደብሮናል፡፡
ት/ቤቱን ያፈረሳችሁት በጣም ያረጀ ነው ብላችሁ ነው አይደል?! ማንም ሳይነግረኝ ነው ያወቅሁት፡፡ ሰርታችሁ ሳትጨርሱ ማፍረሳችሁ እኔ ግን ማመን አቃተኝ፡፡
ሚኪ፤ 5ኛ ክፍል



Read 1135 times