Monday, 15 November 2021 00:00

ኮሮና ከ8 ሚሊዮን በላይ የፕላስቲክ ቆሻሻ ፈጥሯል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የኮሮና ወረርሽኝ ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በመላው አለም በሚገኙ 193 አገራት ውስጥ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ከ8 ሚሊዮን በላይ የፕላስቲክ ቆሻሻ መፈጠሩንና አብዛኛው ቆሻሻም በውቅያኖሶች ውስጥ እንደተጣለ አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
በውቅያኖስ ውስጥ ከተጣለው 26 ሺህ ሜትሪክ ቶን ያህል የፕላስቲክ ቆሻሻ መካከል ከ70 በመቶ በላይ የሚሆነው ከሆስፒታሎች የወጣ እንደሆነና ቆሻሻው ለውሃ አካላት ስነምህዳር ከፍተኛ አደጋ የሚያስከትል ነው መባሉንም ዘገባው አመልክቷል፡፡ የቻይናና የአሜሪካ ተመራማሪዎች በጋራ የሰሩትን ጥናት ዋቢ አድርጎ ዘገባው እንዳለው፣ ኮሮናን ለመከላከል ሲባል ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ቁሳቁሶች እጅግ ከፍተኛ መጠን ያለው ቆሻሻ እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡
በአለም ዙሪያ ከተመረተው የፕላስቲክ ቆሻሻ መካከል 72 በመቶ ያህሉ ከእስያ አገራት የወጣ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ እስከ ሃምሌ ወር ድረስ በአለም ዙሪያ ከኮሮና ጋር በተያያዙ የፕላስቲክ ቆሻሻዎች ሳቢያ እንስሳት ለሞት የተዳረጉባቸውና የተጎዱባቸው 61 ያህል ክስተቶች መመዝገባቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 2692 times