አጫጭር ቪዲዮችን ለማጋራት የሚያስችለውና በአለማቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተወዳጅነትን በማትረፍ ላይ የሚገኘው ቲክቶክ በጥቅምት ወር ብቻ ከ57 ሚሊዮን ጊዜያት በላይ በተጠቃሚዎች ዳውንሎድ መደረጉንና ላለፉት 10 ተከታታይ ወራት በብዛት ዳውንሎድ በመደረግ ቀዳሚው የአለማችን አፕሊኬሽን መሆኑን ቴክ ኒውስ ዘግቧል፡፡
ቻይና ሰራሹ አፕሊኬሽን ባለፈው አመት 2020 በብዛት በመደረግ ቀዳሚው የአለማችን አፕሊኬሽን እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ አፕሊኬሽኑ ባለፈው ወር በብዛት ዳውንሎድ ከተደረገባቸው አገራት መካከል ቻይና እና አሜሪካ እንደሚገኙበትም አመልክቷል፡፡
በጥቅምት ወር ብቻ 56 ሚሊዮን ያህል ጊዜ ዳውንሎድ የተደረገው ኢንስታግራም ከቲክቶክ በመቀጠል በወሩ በብዛት የተደረገ ሁለተኛው አፕሊኬሽን መሆኑ የተነገረ ሲሆን፣ ፌስቡክ፣ ዋትሳፕና ቴሌግራም እንደ ቅደም ተከተላቸው እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ