Saturday, 20 November 2021 14:30

ቻይና አሜሪካን በመብለጥ ቀዳሚዋ የአለማችን ሃብታም አገር ሆነች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    አጠቃላዩ የአለማችን ሃብት 514 ትሪሊዮን ዶላር ደርሷል

           የአለማችን አጠቃላይ ሃብት ከ20 አመታት በፊት ከነበረበት 156 ትሪሊዮን ዶላር በሶስት እጥፍ ያህል በማደግ በ2020 የፈረንጆች አመት 514 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱንና ቻይና አሜሪካን በመብለጥ ቁጥር አንድ የአለማችን ሃብታም አገር ለመሆን መብቃቷን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
ታዋቂው የጥናት ተቋም ማካንሲ ሰሞኑን ያወጣውን አለማቀፍ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ከ20 አመታት በፊት አጠቃላይ ሃብቷ 7 ትሪሊዮን ዶላር ብቻ የነበረው ቻይና ኢኮኖሚዋን በከፍተኛ ፍጥነት በማሳደግ በ2020 አጠቃላይ ሃብቷን 120 ትሪሊዮን ዶላር በማድረሷ አሜሪካን በመብለጥ ቁጥር አንድ የአለማችን ባለጸጋ አገር ለመሆን በቅታለች፡፡
አሜሪካ በ20 አመታት ውስጥ አጠቃላይ ሃብቷን በሁለት እጥፍ ያህል በማሳደግ 90 ትሪሊዮን ዶላር ብታደርስም፣ የአንደኝነት ደረጃዋን ለቻይና ለቅቃ ወደ ሁለተኛነት ዝቅ ማለቷን ነው ዘገባው ያመለከተው፡፡   
ከአጠቃላዩ የአለማችን ሃብት 68 በመቶውን የሚይዘው የሪልእስቴት ዘርፍ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ በአለማቀፍ ደረጃ የሃብት ክፍፍል ሚዛናዊ አለመሆኑንና በቻይናም ሆነ በአሜሪካ ከአጠቃላዩ አገራዊ ሃብት 67 በመቶ ያህሉን የያዙት 10 በመቶ የሚሆኑት የአገራቱ ባለጸጋ ቤተሰቦች እንደሆኑም አመልክቷል፡፡

Read 3516 times