በአለማቀፍ ደረጃ ተወዳጅነትን ያገኘው ቲክቶክ የተባለው የአጫጭር ቪዲዮዎች ማጋሪያ አፕሊኬሽን በፈረንጆች አመት 2021 በብዛት የተጎበኘ የአለማችን ቀዳሚው ድረገጽ በመባል ከጎግል ክብሩን መቀበሉ ተነግሯል፡፡
ክላውድፍሌር የተባለ ተቋም ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘ ጋርዲያን እንደዘገበው፣ ባለቤትነቱ የቻይናው ኩባንያ ባይትዳንስ የሆነው ቲክ ቶክ ካለፈው አመት የካቲት ወር ጀምሮ በጎብኝዎች ብዛት ቀዳሚነቱን በመያዝ በ1ኛነት አመቱን ማጠናቀቅ ችሏል፡፡
ባለፈው አመት በኢንተርኔት በብዛት በመጎብኘት የ7ኛ ደረጃ ላይ የነበረው ቲክ ቶክ ዘንድሮ ግን የአምናውን መሪ ጎግል ወደ ሁለተኛነት ዝቅ በማድረግ ቀዳሚነቱን መያዙን የጠቆመው ዘገባው፣ ቲክ ቶክ ከ1 ቢሊዮን በላይ ወርሃዊ ተጠቃሚዎችን ለማፍራት መቻሉንም አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል