ለ94ኛ ጊዜ የሚካሄደው የኦስካር አካዳሚ ሽልማት ዕጩዎች ባለፈው ማክሰኞ ይፋ የተደረጉ ሲሆን፣ በኔትፍሊክስ አማካይነት ለእይታ የበቃው ‹ፓዎር ኦፍ ዘ ዶግ› 12 ጊዜ በመታጨት በብዛት የታጨ ቀዳሚው ፊልም ሆኗል፡፡
‹ፓዎር ኦፍ ዘ ዶግ› ምርጥ ፊልምና ምርጥ ዳይሬክተርን ጨምሮ 12 ጊዜ ለዘንድሮው ኦስካር ሽልማት በመታጨት ነው 1ኛ ደረጃን የያዘው፡፡
በዋርነር ብሮስ ኩባንያ ለእይታ የበቃው ‹ዱኒ› በበኩሉ 10 ጊዜ በመታጨት ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፣ ቤልፋስት እና ዌስት ሳይድ ስቶሪ እያንዳንዳቸው 7 ጊዜ በመታጨት ሶስተኛ ደረጃ መያዛቸው ተነግሯል፡፡
የዘንድሮው ኦስካር ሽልማት ስነስርዓት በመጋቢት ወር መጨረሻ በዶልቢ ቲያትር በደማቅ ሁኔታ ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
‹ዘ ትራጄዲ ኦፍ ማክቤዝ› በተሰኘው ፊልም ባሳየው ድንቅ ትወናው ለዘንድሮው ኦስካር በምርጥ ተዋናይነት ዘርፍ ለሽልማት የታጨውና በአጠቃላይ ለ10ኛ ጊዜ ለኦስካር የታጨው ዴንዝል ዋሽንግተን ለኦስካር በብዛት በመታጨት ቀዳሚው ጥቁር የፊልም ተዋናይ በመሆን ታሪክ መስራቱ ተነግሯል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል