በባንኮች የተፈጠረው መተረማመስ የማን ጥፋት ነው?!
ብሔራዊ ባንክ ሁሉም ባንኮች የደንበኞቻቸውን መረጃ እንዲያሟሉ በቅርቡ ያወጣው መመርያ ቀነ ገደቡ በመተላለፉ ባንኮች ሌላ አገልግሎት መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ እየተተራመሱ ነው። ሕዝቡም እንደፈረደበት የገዛ ገንዘቡ ታግቶበት፣ በጠራራ ጸሃይ ሰልፍ ተራ ገብቶ እየተተራመሰ ነው። ለማን አቤት ይባላል?!
ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ የተከማቹና በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደንበኞችን መረጃ የማሰባሰብ ውዝፍ ስራ በወራት እንደማይገባደድ እየታወቀ፣ ቀኑን ከማራዘም ይልቅ የሕዝቡን ገንዘብ አግቶ ማተራመስ፣ ሕዝብ እንደለመደው ይሰለፋል እንጂ ምን ያመጣል የሚል ንቀት ይመስላል።
የሀገራችን ተቋማት ስራቸውን በእቅድና በአግባቡ ከመስራት ይልቅ ስራን ለዘመናት ወዝፈው እየኖሩ በድንገት ከእንቅልፉቸው ሲነቁ፣ ሕዝብ ላይ ሱሪ ባንገት ቀጭን ትዕዛዝ እየጫኑ ማተራመሳቸውን የሚያቆሙት መቼ ነው?
በንዝህላልነታቸውስ ምክንያት ሕዝቡ ለሚደርስበት መጉላላት ተጠያቂነታቸው የት ድረስ ነው? የኢትዮጵያ ሕዝብስ ለስንቱ ተቋም አምባገነንነት ጎበስ ቀና እያለ ይኑር?
(ሙሼ ሰሙ)
Published in
ባህል
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል