እስከ ጊዜው ድረስ
እስከ ጊዜው ድረስ
በተያዘው ሳቁ - ከማይቀረው ራቁ
ወረፋ ነውና ተራችሁን ጠብቁ
ይመስላል የማይፈርስ
ጥበቃም የማይደርስ
ሀዘንም የማይመር
ምኞትም የማይሰምር
የረገበ ሁሉ - ዝንታለም የማይከር
የማይመስል ይመስላል!
ግን፤ ድንጋይም በሂደት
እንደ ወይን ይበስላል
ፀሀይዋም አንድ ቀን
ቀይ ድዷ ይከስላል
ጊዜ አረፋ ነው
ባላ’ረፋ ወንዝ ነው
የማይደርስ ይመስላል
ስቆ ያሳስቃል
ተራ ያስጠብቃል፡፡
(ሌሊሣ ግርማ)
Published in
የግጥም ጥግ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል