Saturday, 26 March 2022 10:03

ለዜጎቻቸው ንፁህ የመጠጥ ውሃ ከሚያቀርቡና የማያቀርቡ ሀገራት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ዜጎቻቸው ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ከማያገኙ የዓለም ሃገራት ኢትዮጵያ በ5ኛ ደረጃ እንደምትገኝ የተገለጸ ሲሆን ከጠቅላላው ህዝብ 12.58 በመቶ ዜጎች ብቻ ናቸው ንጹህ ውሃ አቅርቦት የሚያገኙት ተብሏል።
የዓለም ጤና ድርጅትና የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) የ2022 የዓለም የውሃ ቀንን አስመልክተው ባወጡት ሪፖርት፤ ከዓለም ሃገራት በየዓመቱ በተለያዩ በሽታዎች ከሚሞቱ 100 ሰዎች አራቱ በንጹህ የመጠጥ ውሃ እጥረት ሳቢያ መሆኑን ጠቁመዋል።
ከዓለም ሃገራት ዝቅተኛ የንፁህ ውሃ መጠጥ ለዜጎቻቸው ያቀርባሉ ተብለው በሪፖርቱ ከተጠቀሱ 10 ሃገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።
ዝቅተኛ የንጹህ መጠጥ ውሃ  አቅርቦት አላቸው ከተባሉት ከእነዚህ ሃገራት ደግሞ ቻድ ቀዳሚዋ ስትሆን ከአጠቃላይ ህዝቧ 5.9 በመቶ ብቻ ነው ንፁህ የመጠጥ ውሃ የሚያገኘው ተብሏል። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠችው የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ደግሞ ከአጠቃላይ ህዝቧ 6.18 በመቶው ንጹህ የመጠጥ ውሃ ሲያገኝ፣ በ3ኛ ደረጃ የተጠቀሰችው ሴራሊዮን ከአጠቃላይ ህዝቧ 10.6 በመቶ፣ በአራተኛ ደረጃ የተቀመጠችው ሩዋንዳ ከአጠቃላይ ህዝቧ 12.10 በአምስተኛ  ደረጃ የምትገኘው ኢትዮጵያ በበኩሏ ከአጠቃላይ  ህዝቧ  12.5 በመቶ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸው ተጠቁሟል።
በዚህ ዝርዝር ውስጥ ኡጋንዳና ዲሞክራቲክ ኮንጎ ከአፍሪካ ተጠቃሽ ሲሆኑ ኪረባቲ፣ ኔፓል እና ላኦስም ይገኙበታል።
ለዜጎቻቸው ንጹህ የመጠጥ ውሃ በማዳረስ ሙሉ ለሙሉ ወይም መቶ በመቶ በማዳረስ ከ1ኛ እስከ 10ኛ ያለውን ቦታ ያገኙት ሃገራት ደግሞ ግሪክ፣ አይስላንድ፣ ኩዌት፣ ላይተንስታይን፣ ማልታ፣ ሞናኮ፣ ኒውዚላንድ፣ ሣን ማሪዮ ሲንጋፖር ሲሆኑ፤ ጀርመን በበኩሏ 99.99 በመቶ ዜጎቿ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸው በሪፖርቱ ተጠቅሷል።
ከጤና አንጻር የንጹህ ውሃ አቅርቦታቸው ዝቅተኛ ናቸው ተብለው የተጠቀሱ ሃገራት 22 በመቶ የህክምና ተቋሞቻቸው በንጹህ ውሃ አቅርቦት የሚቸገሩ እንደሆነ ያመለከተው ሪፖርቱ፤ ከንጹህ ውሃ ማጣት ጋር በተያያዘም ታካሚዎች ተገቢውን ህክምና ባለማግኘት ጭምር ህይወታቸው እንደሚያልፍ ኒውዚ ተመልክቷል።

ንፁህ የመጠጥ ውሃ
 (5.9 %-12.58 %)    ንፁህ የመጠጥ ውሃ (100 %)
- ቻድ
- ሴራሊዮን
- ኢትዮጵያ
- ኡጋንዳ
- ሩዋንዳ
- ኔፓል - ግሪክ
- አይስላንድ
- ኩዌት
- ማልታ
- ሞኖኮ
- ኒውዚላንድ
- ሲንጋፖር


Read 11847 times