Print this page
Tuesday, 29 March 2022 00:00

አድማስ ትውስታ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በደግነት የተንቆጠቆጠ ልብ! (የቅጣት ትኬት ወይስ የፍቅር ትኬት?!)



             የ28 ዓመቱ ዴል የ3 ዓመት ህፃን ልጁን ጨምሮ ቤተሰቡን በመኪናው ጭኖ በአሜሪካ ዌስትላንድ ግዛት አውራ ጎዳና ላይ እያሽከረከረ ነበር እ.ኤ.አ በ2016 ሰኞ ቀን።
ዴል መኪናውን እያሽከረከረ ከሰጠመበት ሰመመን የነቃው የፖሊስ መኮንን ድንገት ሲያስቆመው ነው። የመኪናው የጎን መስታወት ዕይታን በሚጋርድ ፕላስቲክ ተሸፍኖ ነበር ጆሱዋ ስካልጂዮን የተባለው የፖሊስ መኮንን ወደ መኪናው ቀርቦ ወደኋላ መቀመጫ ሲመለከት የ3 ዓመት ህጻን ልጁ  ደህንነት መጠበቂያ ወንበር ነው የተቀመጠችው፡፡ የህጻን ልጁን ህይወት ለአደጋ አጋልጦ መኪና ለማሽከርከር መድፈሩ ሳያስገርመው አልቀረም። “ጌታው፤ ህፃን ልጅህን እንዴት ያለ ደህንነት መጠበቂያ ወንበር ጭነሃት ትዞራለህ?” ሲል ጠየቀው አሽከርካሪውም፤ “ምን መሰለህ የዕዳ መዓት ተከምሮብኝ የደህንነት ወንበሩን የምገዛበት ገንዘብ አጥቼ ነው አለው፡፡
የፖሊስ መኮንኑ፣ ዴል ከመኪናው እንዲወጣ ጠየቀው ንግግራቸውን ቤተሰቡ እንዲሰማ አልፈለገም፡፡ ዴል ግን በሌለኝ ገንዘብ የቅጣት መዓት ሊጭንብኝ ነው በሚል ደንግጦ ነበር፡፡ ዴል ከመኪናው ከወረደ በኋላ የደረሰበትን የኑሮ ፈተና አሁን ያለበትን ሁኔታ፤ የሚጠበቀውን የተከመረበትን የዕዳ መጠንና፤ የገጠመውን የገንዘብ እጥረት ለፖሊሱ በዝርዝር ነገረው። “ወንድሜ፤ ወደ ዎልማርት ተከትለኸኝ ልትመጣ ትችላለህ?” አለው የፖሊስ መኮንኑ- ዴልን። “ለምን?” በድንጋጤና ግራ በተጋባ ስሜት ጠየቀ፤ ዴል።
“የህፃናት የደህንነት መጠበቂያ ወንበሩን ደስ እያለኝ ልገዛልህ እወዳለሁ” መለሰለት ፖሊሱ ዴል ጆሮውን ማመን አልቻለም። ፖሊሱን ተከትሎ ወደ ተባለው መደብር ለመከተል ከመንቀሳቀሱ በፊት ጥቂት አፍታ መውሰድ ነበረበት- ለመረጋጋት።
ዴል እና ስካልጂዮኒ ወደ ሸቀጥ መደብሩ ሲጓዙ፣ ስለ ህይወት ተሞክሯቸው በጥልቀት እያወጉ ነበር።
“ሁለታችንን ዎልማርት ውስጥ ድንገት የተመለከተን ሰው የረዥም ጊዜ ምርጥ ጓደኛሞች መሆናችንን ፈጽሞ አይጠራጠርም።”  ሲል ዴል ጽፏል-በፌስ ቡክ ገፁ።
ስካልጂዮኒ ህፃኗ የምትወደውን ፒንክ ቀለም ያለው ፒንክ-የደህንነት መጠበቂያ ወንበር ነበር የገዛው- ያውም በቢራቢሮዎች ያሸበረቀ ያጌጠ።
ዴል “ከዚህ ቀደም ከገጠሙት ፖሊሶች ሁሉ የተለየ መሆኑን ለስካልጂዮኒ እንደነገረው ይገልጻል። የስካልጂዮኒ መልስ ግን ቀለል ያለ ነበር- “እኔ ሥራዬን ብቻ ነው የሰራሁት” ሲል መለሰለት።
“የቅጣት ትኬት ብቆርጥልህ አንተን የባሰ መከራ ውስጥ ከመዝፈቅ ውጭ ፋይዳ የለውም ብዬ ነው” እንዳለውም ዴል ያስታውሳል።
አዲሱን የህጻናት የደህንነት መጠበቂያ ወንበር መኪናው ውስጥ በደስታ ተሞልቶ ከገጠመ በኋላ  ነበር ዴል ለካስ የዚህን ደግ ፖሊስ ስም እንደማያውቅ የተገነዘበው።
ይሄን ጊዜ ነው የሆነውን ሁሉ በፌስቡክ ለማጋራትና የፖሊስ መኮንኑን የደግነት ተግባር ዕውቅና በመስጠት ለዓለም ለማስተዋወቅ የወሰነው። ታሪኩም በማህበራዊ ሚዲያ በአስደናቂ ፍጥነት ተሰራጨ። የዌስትላንድ ፖሊስ መምሪያ ዘንድም ደረሰ። ፖሊስ መምሪያው ግን ይሄንን የደግነት ተግባር የፈጸመው የትኛው የፖሊስ መኮንን እንደሆነ ለማወቅ በቀላሉ አልቻለም። ለምን ቢሉ? ስካሊጅዮ ይህን በጎ ስራውን ለማንም ትንፍሽ አላለም ነበር።
“የሱ ብቸኛ ዓላማ አሽከርካሪውን መርዳት እንጂ ዕውቅና ማግኘት አልነበረም” ሲል የፖሊስ መምሪያው በፌስቡክ ገፁ ባሰፈረው መግለጫው ጠቁሟል፡፡
የፖሊስ መምሪያው ለስካልጂዮን ውዳሴና ሙገሳ ያቀረበ ሲሆን፤ ዴልንም አመስግኗል- ተሞክሮውን በማጋራቱ።
“በአሉታዊ ታሪኮች በተሞላ ዓለም ውስጥ ያንተን በጎ ታሪክ ማጋራትህ በሁላችንም ላይ የማይታመን በጎ ተፅዕኖ ያሳድርብናል።” ብሏል- የፖሊስ መምሪያው- በመግለጫው።
የዌስትላንድ ፖሊስ መምሪያ ይሄን በጎ ተግባር የፈጸመው ስካልጂዮኒ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ ከዴል ጋር ዳግም የሚገናኙበትን ቀን ፈጥሯል- በመመሪያው ቅጥር ግቢ። በነገራችን ላይ ታዋቂው አሜሪካዊ የቲቪ ሾው አዘጋጅ፣ ኮሚዲያንና ደራሲ ስቲቭ ሃርቬይ፤ ዴልንና ስካጂዮን በታዋቂው የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ እንግዶች አድርጎ አቅርቧቸው ነበር-ሌሎች ከታሪኩ ትምህርት እንዲወስዱ። በርግጥም ልብን የሚያሞቅ የደግነት ተግባር ነው የፖሊስ መኮንኑ የፈጸመው። የቅጣት ትኬት ይቆርጣል ተብሎ ሲጠበቅ፣ የፍቅር ትኬት ቆርጦ መላ ታሪኩን ለወጠው፡፡


Read 8186 times
Administrator

Latest from Administrator