Saturday, 02 April 2022 12:14

50 ሚሊዮን ህንዳውያን ለ2 ቀናት የስራ ማቆም አድማ መቱ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የህንድ መንግስት ያወጣውን ሰራተኞችን የሚጎዳ አዲስ ህግ የተቃወሙ 50 ሚሊዮን ያህል የአገሪቱ ዜጎች ባለፈው ሰኞ እና ማክሰኞ የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸው ተዘግቧል፡፡
የባንክ፣ የፋብሪካና የህዝብ ትራንስፖርት ሰራተኞችን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ተቀጥረው የሚሰሩ ዜጎች በአገሪቱ ስድስት ግዛቶች በስራ ማቆም አድማው ላይ እንደተሳተፉም ዴይሊ ሜይል አስነብቧል፡፡
መንግስት በቅርቡ ያወጣው ህግ የሰራተኞችን መብቶችና ጥቅማጥቅሞች የሚጻረር በመሆኑ ሊስተካከል ይገባል፤ ዝቅተኛ ደመወዝ ከፍ ሊል ይገባል፣ የማህበራዊ ዋስትና ይሰጠን በሚል በተጠራው የስራ ማቆም አድማ ላይ ከ200 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ቢጠበቅም ያን ያህል ቁጥር አለመመዝገቡን የጠቆመው ዘገባው፤ አድማው ተጽዕኖ የማድረስ አቅሙ ግን አነስተኛ ነው መባሉን አመልክቷል፡፡


Read 2031 times