Tuesday, 19 April 2022 00:00

በሶማሊያ “የሴቶች ብቻ” ሚዲያ ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ሙሉ ለሙሉ በሴቶች ብቻ የሚንቀሳቀስና የራሱ የሆነ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ያሉት ቢላን የተሰኘ አዲስ የሚዲያ ተቋም ተመስርቶ  ስራ መጀመሩ ተነግሯል፡፡
ሚዲያው ሴቶችን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራና ለሴቶች መብቶች መከበር የሚታገል እንደሆነ የዘገበው ቮይስ ኦፍ አሜሪካ፤ ከጋዜጠኞች እስከ አስተዳደር ሰራተኞች ሙሉ ለሙሉ በሴቶች ብቻ የሚንቀሳቀስ እንደሆነና የተለያዩ ፈተናዎች ለሚያጋጥሟቸው የሶማሊያ ሴት ጋዜጠኞች መልካም እድል እንደሚፈጥርም አመልክቷል፡፡
ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተቋቋመው ቢላን ሚዲያ፣ በመጪዎቹ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስርጭቱን ይጀምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆመው ዘገባው፤ የሴቶች ጥቃት፣ የፖለቲካ ተሳትፎ፣ የስራ ፈጠራና የመሳሰሉ ጉዳዮችን የተመለከቱ ይዘቶችን እንደሚያቀርብም አመልክቷል፡፡


Read 7957 times