Print this page
Sunday, 24 April 2022 00:00

61 በመቶ የአለም ህዝብ የዩክሬን ጦርነት አገሬን ክፉኛ ይጎዳታል ብሎ እንደሚያምን ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    - 72 በመቶው አገሬ በጦርነቱ ውስጥ መሳተፍ የለባትም ይላል
      - 66 በመቶው በሩስያ ላይ ማዕቀብ መጣል ይበጃል ይላል

            አይፒኤስኦኤስ የተባለ አለማቀፍ የጥናት ተቋም የሩስያና የዩክሬን ጦርነት በተቀረው አለም ዘንድ የፈጠረውን ስጋት ለማወቅ በሰራው ጥናት 61 በመቶ የአለም ህዝብ የዩክሬን ጦርነት አገሬን ክፉኛ ይጎዳታል ብሎ እንደሚያምን ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
ተቋሙ በተመረጡ የአለማችን አገራት የሰራውን ጥናት መሰረት አድርጎ ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ሪፖርት እንዳለው፣ ጥናቱ በተደረገባቸው አገራት ከሚኖሩ ሰዎች መካከል 70 በመቶ ያህሉ የሁለቱን አገራት የተመለከቱ ዜናዎችንና መረጃዎችን በንቃት እንደሚከታተሉ ተናግረዋል፡፡
ጥናቱ በተደረገባቸው ሁሉም አገራት 74 በመቶ የሚሆነው ህዝብ መንግስታችን የዩክሬንን ስደተኞች መቀበል አለበት ብሎ እንደሚያምን፤ 72 በመቶ የሚሆነው ደግሞ አገሬ በጦርነቱ ውስጥ መሳተፍ የለባትም ብሎ እንደሚያምን ማረጋገጡንም ሪፖርቱ ያሳያል፡፡
በጥናቱ ከተሳተፉት ሰዎች መካከል ከ66 በመቶ በላይ የሚሆኑት የምዕራቡ አለም በሩስያ ላይ የሚጥላቸው ማዕቀቦች ጦርነቱን በማስቆም ረገድ ውጤታማና ጠቃሚ ናቸው ብለው እንደሚያምኑ የሚያመለክተው ሪፖርቱ፣ ተጨማሪ ማዕቀቦች ያስፈልጋሉ ብለው የሚያምኑት ግን 48 በመቶ ያህሉ ብቻ መሆናቸውን ያብራራል፡፡

Read 2801 times
Administrator

Latest from Administrator