Tuesday, 26 April 2022 00:00

አለማቀፉ የሞባይል ሽያጭ በ11 በመቶ መቀነሱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ሳምሰንግ በ24 በመቶ የገበያ ድርሻ 1ኛ ደረጃን ይዟል

          ከሩስያና ዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ የፈረንጆች አመት 2022 የመጀመሪያው ሩብ አመት አለማቀፍ የሞባይል ስልኮች ሽያጭ በ11 በመቶ ያህል ቅናሽ በማሳየት ወደ 272 ሚሊዮን ዝቅ ቢልም፣ ሳምሰንግ በሽያጭ መሪነቱን መያዙ ተነግሯል፡፡
ካናሊስ ቪፒ የተባለው አለማቀፍ የጥናት ተቋም ባለፈው ረቡዕ ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርት እንዳለው፣ ከጦርነቱ በተጨማሪ ለሽያጩ መቀነስ ሰበብ ከሆኑት ጉዳዮች መካከል የዋጋ ንረት በአለማቀፍ ደረጃ መባባሱና በቻይና የኮሮና ቫይረስ የእንቅስቃሴ ገደቦች መቀጠላቸው እንደሚገኙበትም ተዘግቧል፡፡
በሩብ አመቱ አለማቀፍ የሞባይል ስልኮች ሽያጭ ቀዳሚነቱን የያዘው የደቡብ ኮርያው የኤሌክትሮኒክስ አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ኩባንያው ከአለማቀፉ ገበያ የ24 በመቶ ድርሻ መያዙንና የአሜሪካው አፕል በ18 በመቶ ድርሻ፤ የቻይናው ዢያኦሚ በ13 በመቶ ድርሻ ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ መያዛቸውንም ያብራራል፡፡

Read 5524 times