አምባሳደር ልብስ ስፌትና ንግድ ኃ.የተ.የግል ማህበር በ500 ሚሊዮን ብር ወጪ ያሰራውን የገበያ ማዕከል (አምባሳደር ሞል) በቅርቡ ያስመርቃል።
በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ፓርላማ ፊት ለፊት የተገነባው አምባሳደር ሞል፤ በቅርቡ ለምረቃ እንደሚበቃ የድርጅቱ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰኢድ መሃመድ ብርሃን ተናግረዋል።
ከ120 መኪኖች በላይ በአንድ ጊዜ ለማስተናገድ የሚችል የመኪና ማቆሚያ እንዳለው በተነገረለት በዚሁ የገበያ ማዕከል፤ በአንድ ሰኮንድ 10 ሊትር ውሃ ለማምረት የሚችል የከርሰ ምድር ውሃ በቁፋሮ እንዲወጣና አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉም ተገልጿል።
አምባሳደር ሞል ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩ ታውቋል።
ከ40 ዓመታት በፊት በአንድ የልብስ ስፌት ማሽን ስራ የጀመረው አምባሳደር ልብስ ስፌት ኃ.የተ.የግ.ማህበር አምባሳደር ሪልእስቴት፣ አምባሳደር ሆቴልና አምባሳደር ሞል የተባሉ ድርጅቶችን ማፍራት ችሏል።