Sunday, 01 May 2022 00:00

ቶዮታ 9.51 ሚሊዮን መኪኖችን በመሸጥ የምንግዜም 2ኛ ክብረወሰኑን አስመዘገበ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የአለማችን ቁጥር አንድ የመኪና አምራች ኩባንያ የጃፓኑ ቶዮታ ሞተር ኮርፖሬሽን እስካለፈው መጋቢት ወር ባለው አንድ አመት 9.51 ሚሊዮን መኪኖቹን ለአለማቀፍ ገበያ ማቅረቡንና ይህም በታሪኩ 2ኛውን ከፍተኛ አመታዊ ሽያጭ ሆኖ መመዝገቡን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
ኩባንያው ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ ከ903 ሺህ በላይ መኪኖቹን መሸጡን፣ በ12 ወራት ውስጥ ያስመዘገበው አጠቃላይ ሽያጭም 9.51 ሚሊዮን መድረሱንና ይህም ከዕቅዱ በላይ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 8.57 ሚሊዮን መኪኖችን ማምረቱን አመልክቷል፡፡
ኩባንያው ምንም እንኳን በአመቱ የግዢ ጥያቄዎች ቅናሽ ቢያሳዩበትም 9.4 ሚሊዮን መኪኖችን ለመሸጥ አቅዶ 9.51 ሚሊዮን መኪኖችን ለመሸጥ መቻሉን የጠቆመው ብሉምበርግ፣ ለሽያጩ ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱት ምርቶቹ መካከልም  በእስያና በሰሜን አሜሪካ ገበያ በብዛት የተሸጡት ራቫ4 ሱቭ ሞዴል መኪኖቹ እንደሚገኙበት ገልጧል፡፡

Read 1033 times