Saturday, 30 April 2022 14:30

የማህጸን መውጣት ማለት ምን ማለት ነው?

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የሴቶች ማህጸን መውጣት ማለት የሴቶች የጀርባ ወይንም የወገብ አጥንት ሲደክም የሚከሰት ችግር ነው፡፡ ይህ እድሜአቸው ከ50-79 አመት የሚደርሱ ከአጠቃላይ ሴቶች ግማሽ የሚያህሉት የሚገጥማቸው ሕመም ነው፡፡ ይህን መረጃ ያወጣው ማዮ ክሊኒክ በ2020/ዓ/ም ነው።
Uterine prolapse የህክምና ቋንቋው ሲሆን prolapse የሚለው ቃል የተገኘው ከግሪክ ነው። ትርጉዋሜውም አንድ ነገር ከነበረበት ወይንም ከተፈጠረበት እና ከሚቀመጥበት ቦታውን ሲለቅ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ቃል ለማህጸን ብቻም ሳይሆን ለተለያዩ አካላትም ይገለግላል። ለምሳሌ በወገብ ላይ የዲስክ መንሸራተት እንዲሁም በብልት ላይ የሚደርሱ መንሸራተቶች ይገለጹበታል፡፡
ማህጸን በአንዲት ሴት Hip joint ወይንም Hip Bon በሚባለው አጥንት ውስጥ ተቀምጦ የሚገኝ ሲሆን ይህ አካል እግራችንን እና የላይኛውን የሰውነት ክፍላችንን የሚያገናኝ የአ ጥንት ክፍል ነው፡፡ ማህጸን የተለያዩ ክፍሎች አሉት፡፡ አንዱ እርግዝናውን የሚሸከም ሌላው እንደበር የሚያገለግል ቱቦ ነው፡፡ እነዚህ ቱቦዎች በየወሩ የሚወጣውን እንቁላል ወደ ማህ ጸን የሚያጉዋጉዙ ናቸው፡፡ የማህጸን ቱቦው፤ የማህጸን ከረጢቱ እና የእንቁላል ከረጢቱ በዚሁ አጥንት ውስጥ ተጣብቀው የሚገኙ ናቸው። የዚህ አካል አቀማመጥ እና የሚያደ ርገው ድጋፍ ማህጸኑ እዛው ቦታ ላይ ሆኖ እንዲቆይ የሚያደርጉ በአካባቢው ያሉ  ጅማቶ ችን፤ ጡንቻዎችን እንዲሁም አጥንቱ እና ነርቮቹ ሁሉ ተዳምረው ማህጸንን ከቦታው ሳይን ቀሳቀስ እንዲኖር ለማድረግ የሚረዱ ናቸው፡፡ የሴት ልጅ ሌሎች አካላት ማለትም የሽ ንት ፊኛ እና ትልቁ አንጀት(ደንዳኔ) ጭምር ከማህጸን ፊትና ሁዋላ የሚገኙ ሲሆን እነ ዚህም ከቦታቸው ወደውጭ ሳይወጡ እንዲኖሩ የሚያደርጉ ድጋፎች በአጥንቱ፤ በጡን ቻው፤ በጅ ማቶች ይደረግላቸዋል፡፡  ጅማቶች አካላቱን ከአጥንቱና ማህጸኑ ጋር በማያያዝ ማህጸኑም ሆነ በአካባቢው ያሉ አካላት ከቦታው ሳይንቀሳቀሱ እንዲኖሩ ያስችሉአቸዋል፡፡
ማህጸን ማለትም ልጅ የሚሸከመው አካል ከፊት ለፊቱ የሽንት ፊኛ እንዲሁም ከሁዋላው ደግሞ ደንዳኔ የተባለው ትልቅ አንጀት ይገኛል። ማህጸን በእነዚህ የውስጥ አካላት አማካ  ኝነት ወደላይ ተደግፎ የሚኖር አካል ነው፡፡ ማህጸን በተፈጥሮው ያገኘውን መደገፊያ ጥን ካሬ በሚያጡበት እና በሚላሉበት ወቅት ማህጸን ወደ ብልት ወደታች እየተገፋ ይመጣል። በዚህ ጊዜ ማህጸን ብቻም ሳይሆን የሽንት ፊኛና ደንዳኔውን ደግፎ የሚይዘው ብልትም ወደውጭ ይወጣል፡፡ ማህጸን ወደውጭ ይወጣል ሲባል አራት ደረጃዎች አሉት። ዶ/ር ዳዊት ደሳለኝ የጽንስና ማህጸን ሕምና እስፔሻሊስት ከአሁን ቀደም እንደነገሩን፡፡
ልጅ የሚሸከመው የማህጸን ክፍል ወደ ብልት መንጠልጠል ይጀምራል፡፡
ማህጸን በብልት አካባቢ ክፍት ወደሆነው ቦታ በመውረድ ይቀመጣል፡፡
ማህጸን በብልት በኩል መውጣት ይጀምራል፡፡
ማህጸን እንዲሁም ብልት ተያይዘው ሙሉ በሙሉ ወደውጭ ይወጣሉ፡፡
የማህጸን ወደውጭ መውጣት በምን ምክንያት ያጋጥማል? ማዮ ክሊኒክም ሆነ ዶ/ር ዳዊት የገለጹት ተመሳሳይ ምክንያቶችን ነው::
ዋናው ምክንያት እድሜ ነው፡፡ ሴቶች በማንኘውም እድሜ የማህጸን መውጣት ሊያጋጥ ማቸው የሚችል ሲሆን በዋናነት ግን እድሜአቸው ለወር አበባ መቋረጥ የደረሰ ሴቶች ላይ ይከሰታል፡፡ በወር አበባ መቋረጥ እድሜ ክልል ያሉ ሴቶች ኢስትሮጂን የሚባለው ቅመም በሰውነታቸው መመረቱን ስለሚያቆም የጡንቻዎች መላሸቅ ይጀምራል፡፡
ሌላው ችግር ከመውለድ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በመውለድ ጊዜ ኪሎአቸው ከበድ ያሉ ልጆችን በመውለድ ወይንም ለረጅም ጊዜ በምጥ ላይ መቆየት እንዲሁም ብዙ ልጆችን መውለድ ለማህጸን መውጣት ችግር ሊያጋልጥ ይችላል፡፡
ልጅ በማዋለድ ወቅት የልጅ ጭንቅላት አልወጣ ሲል ወይንም በተለያየ ምክንያት ለመርዳት ሲባል የሚጠቀሙበት ዘዴ ለማህጸን ከቦታው መልቀቅ ምክንያት ሊሆን የሚችልበት አጋ ጣሚ መኖሩም በባለሙያዎች ይገለጻል፡፡  
ከፍተኛ የሆነ ውፍረት ለማህጸን መውጣት ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ ውፍረት በራሱ በማህጸን አካባቢ ያሉ ጡንቻዎችን እንዲላሉ ማድረግ ስለሚችል ጥንቃቄ ያስፈልጋል፡፡ የሆድ እቃ ግፊት መብዛትም ለማህጸን መውጣት እንደ አንድ ምክንያት ይወሰዳል፡፡
እንደ ሳል፤የሆድ ድርቀት የመሳሰሉተ ሕመሞችም ለማህጸን መውጣት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
የማህጸን መውጣት ሲያጋጥም ምን አይነት ስሜቶች ይኖራሉ?
የወገብ አጥንት ላይ ክብደት ወይንም የመጎተት ስሜት ይኖራል፡፡
በብልት በኩል ጎልቶ የሚወጣ ስጋ መሰል ነገር መኖሩ ይሰማል፡፡
ሽንትን በመሽናት በኩል በትንሽ ትንሽ (ጭርቅ ጭርቅ)እንደሚባለው ወይንም የመሽናት ሁኔታ መዘግየት ሊኖር ይችላል፡፡
በትንሽ ኳስ ላይ እንደተቀመጡ ወይንም ከብልት ውስጥ አንድ ነገር እየወደቀ እንዳለ ያለ ስሜት ሊሰማ ይችላል፡፡
ወሲባዊ ግንኙነትን በሚመለከት በብልት አካባቢ ያለው ስሜት ሴትየዋ ወሲብን እንደማት ፈልግ፤ወይንም ያ የፍላጎት ስሜትዋ እንደተቋረጥ አድርጋ እንድታስብ የሚያደርግ ነው፡፡
ከላይ የተጠቀሱት ስሜቶች ምናልባትም በጠዋቱ ጊዜ ብዙም የማይሰሙ ቢሆኑ እንኩዋን ቀኑ እየጨመረ ወይንም እየመሸ ሲሄድ ግን ጭንቀቱ እና መረበሹ እየጨመረ ይሄዳል፡፡ በጠዋቱ ጊዜ ህመሙ ላይሰማ ይችላል ማለትም ሌሊቱን በመኝታ ስለሚያሳልፉ በመጠኑ መረጋጋት ስለሚኖር ሊሆን ይችላል፡፡ የማህጸን መውጣት አይነት ሕመም በአንዳንድ በወገብ (የደም ጋን) አካባቢ ባሉ የውስጥ አካላት ላይም ይከሰታል፡፡  
ለምሳሌም የሽንት ፊኛን እና የሴት ብልትን ለያይተው የሚይዙ ጡንቻዎች ወይም ጅማቶች ድክመት ወይንም መላላት፤ መሳሳት ሲገጥማቸው የሽንት ፊኛው በማበጥ ወደ ብልት ሊንሸራተት ይችላል፡፡ Anterior Prolapse (systocele) በመባል የሚታወቀው መንሸራተት የሽንት ፊኛ መንሸራተት በሚል ይታወቃል፡፡
ሌላው በህክምናው ቋንቋ Posterior vaginal prolapse (rectocele) የሚባለው ነው፡፡ ይህ ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ ፊንጢጣን እና ብልትን ከፍሎ ለየብቻቸው እንዲሆኑ የሚይዘው ጡንቻ ወይንም ጅማት መላላት ወይንም መድከም የሚያመጣው የብልት መንሸራተት ችግር ነው፡፡
የማህጸን መውጣት አስከፊ ገጽታው ብልት ላይ በሚያደርገው ግፊት የተነሳ የብልትን ቅር ጹን ወይንም አቀማመጡን በማበላሸት ማህጸኑ ወደታች በመገፋት በብልት በኩል ጎልቶ በመውጣት ተፈጥሮአዊ ሁኔታውን መለወጡ ነው፡፡ በብልት አካባቢ የሚለበሱ ልብሶች ጋር በሚፈጠረው መነካካት ወይንም መፈጋፈግ የተነሳ ከብልት ተንሸራቶ በወጣው አካል ላይም ጭምር መቁሰል ፤መድማት መከሰቱ ሌላው አስከፊ ገጽታው ነው፡፡ ቁስለት ሲከሰት በሚፈ ጠረው ኢንፌክሽን ምክንያት ሴትየዋ ሕክምና ካላገኘች ከፍተኛ ወደሆነ ጉዳት ልትገባ ትችላለች፡፡
የማህጸን መውጣት እንዳይከሰት አስቀድሞ መከላከል ይቻላል፡፡
የአካል እንቅስቃሴ ማድረግ በተለይም በብልት አካባቢ ወይንም በወገብ አካባቢ ያሉ የሰውነት ክፍሎችን መርዳት ፤ማጠንከር በመሳሰለው ሁኔታ በብልት አካባቢ ያሉ ጡንቻዎችን ለማጠ ንከር መሞከር ይጠቅማል፡፡ በተለይም ልጅ ከወለዱ በሁዋላ በማህጸን ዙሪያ ያሉ ጡንቻዎች እንዲጠነክሩ ማድረግ ጠቃሚ ነው፡፡
የሆድ ድርቀትን ለመከላከል ፈሳሽን መጠጣት፤ ምቹ የሆኑ ሆድን የሚያለሰልሱ (ፍራፍሬ፤ አትክልት፤ ባቄላ፤ የመሳሰሉ ምግቦችን መመገብ ይጠቅማል፡፡
ከፍተኛ ሳልን መቆጣጠር ያስፈልጋል ፡፡ እንደ ብሮንካይትስ ያለ ህመምን በህክምና መርዳት በሚከሰተው ሳል ምክንያት የሚኖረውን ግፊት ይከላከላል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም ሳልን ለመቀነስ ወይም እንዳይከሰት ለማድረግ ሲጋራ ማጤስን ማቆም ይመከራል፡፡
ከፍተኛ ውፍረትን ማስወገድ የማህጸን መውጣት ችግር እንዳይመጣ ይረዳል፡፡

Read 13637 times