Saturday, 21 May 2022 11:41

የ4ሺ ብር በርገር በሞባይል ያዘዘው ህፃን

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት ውስጥ ነው።የሁለት ዓመቱ ህፃን ባሬት ጎልደን ሁልጊዜ በእናቱ የሞባይል ስልክ መጫወት ይወዳል። እናቱ እንደምትለው፤ በሞባይል ስልኩ ራሱን ፎቶግራፍ እያነሳ ይዝናናል፡፡ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ  ግን ራሱን ፎቶ በማንሳት ብቻ አልተወሰነም፡፡ እናቱን ላልታሰበ የገንዘብ ኪሳራ ዳርጓል፤ያውም የኑሮ ውድነት ጣራ በነካበት በዚህ ወቅት፡፡ ባሬት ጎልደን ድንገት በተጫነው ቁልፍ 91 ዶላር (4550 ብር ገደማ) ክፍያ ፈፅሞ 31 ቺዝ በርገሮች ያዘዘ ሲሆን 16 ዶላር (900 ብር ገደማ) ቲፕም (ጉርሻ) መስጠቱን ስካይ ኒውስ ዘግቧል፡፡
 እናት እንደተናገረችው፣ የሞባይል ስልኳን የቆለፈችው (ሎክ ያደረገችው) ነበር የመሰላት፡፡ ነገር ግን አለመቆለፏን ያወቀችው የታዘዙት 31 ቺዝ በርገሮች ተጠቅልለው ቤቷ ድረስ ሲመጡላት ነው፡፡ የ4550 ብር ቺዝ በርገሮች!
 በደቂቃዎች ውስጥ ከ5 ሺ ብር በላይ ኪሳራ የደረሰባት የህጻኑ እናት ወዲያው ሞባይል ስልኳን እንደቆለፈች የዘገበው ስካይ ኒውስ፤ ቺዝ በርገሮቹም ለጎረቤት ተከፋፍለዋል ብሏል፡፡

Read 1667 times