Saturday, 21 May 2022 12:52

የቻይናዋ ኡጉር በጅምላ በማሰር ከአለም 1ኛ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ኡጉር የተባለችዋ የቻይና ግዛት በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎችን እያፈሰች በገፍ ወደ እስር ቤት በማጋዝ በመላው አለም አቻ እንደማይገኝላት በመረጃ መረጋገጡንና ከግዛቷ 25 ነዋሪዎች አንዱ በሽብርተኝነት ተከስሶ በእስር ቤት እንደሚገኝ ዘ ጋርዲያን ከሰሞኑ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
አሶሼትድ ፕሬስ አገኘሁት ያለውን መረጃ መሰረት አድርጎ በዘገባው እንዳለው፣ ኡጉር በተባለችውና ሙስሊሞች በሚበዙባት የቻይና ግዛት ህጻናትና አረጋውያንን ጨምሮ ከ10 ሺህ በላይ ሰዎች በሽብር ተከስሰው በእስር ላይ እንደሚገኙና ከ2 እስከ 25 አመት በሚደርስ እስር እንደተቀጡ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡መረጃው የቻይና መንግስት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን በተለያዩ ሰበቦች በእስር ቤት አጉሮ ይገኛል የሚለውን ውንጀላ የሚያጠናክር ነው መባሉን የጠቆመው ዘገባው፤ መንግስት በተለይ አናሳ ሙስሊሞች በሚበዙባት ኡጉሩ እየፈጸመው የሚገኘውን የጅምላ እስርም የሚያረጋግጥ ነው ብሏል፡፡

Read 995 times