Print this page
Saturday, 04 June 2022 14:46

የጋዜጠኛና ገጣሚ የምስራች አጥናፉ “ንጉስ ሃሳብ” የግጥም መድበል ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“ንጉስ ሃሳብ” የተሰኘው የጋዜጠኛና ገጣሚ የምስራች አጥናፉ የግጥም መድበል፣ ዛሬ ግንቦት 27 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት ይመረቃል፡፡
በጋዜጠኛዋ የግጥም መድበል ምረቃ ስነ ስርዓት ላይ ከጣሊያን ኤምባሲ የ30 ዓመታት ቆይታ በኋላ የተለቀቁት ሌ/ጄኔራል አዲስ ተድላ፣ የኢዜማ ሊቀመንበር የሺዋስ አሰፋ፣ የህግ ባለሙያና የሰብአዊ መብት ተከራካሪው አቶ ወንድሙ ኢብሳ፣ የኢዜማ ም/ሊቀመንበር አንዷለም አራጌን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች በክብር እንግድነት እንደተጋበዙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ጋዜጠኛና ገጣሚ የምስራች አጥናፉ ከዚህ ቀደም በሬዲዮ ፋና፣ በናሁ ቴሌቪዥን፣ በዋልታ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ ፕሮግራሞችን በማቅረብ የምትታወቅ ሲሆን በኢሳት ቴሌቪዥንም በተለየ ሁኔታ ለሃገር አበርክቶ ያላቸውን ግለሰቦች በመጋበዝ በምታዘጋጀው የቃለ ምልልስ ፕሮግራም ትታወቃለች፡፡

Read 11347 times
Administrator

Latest from Administrator