Saturday, 18 June 2022 17:24

“ምን ልታዘዝ አዲስ” የሞባይል መተግበሪያ ሥራ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

  አገልግሎት ሰጪና ፈላጊን ያገናኛል ተብሏል

                አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን ከአገልግሎት ፈላጊዎች ጋር የሚያገናኝና አስተማማኝ አገልግሎት ያቀርባል የተባለ ሞባይል መተግበሪያ ተመርቆ ስራ ጀመረ።
በትናንትናው ዕለት በይፋ ስራውን የጀመረውና “ምን ልታዘዝ አዲስ” የተሰኘው ይኸው መተግበሪያ፤ የኮንስትራክሽን ባለሙያዎችን፣ የፍሳሽ ውሃ መስመር ዝርጋታ፣ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታና፣ የዲሽ ስራ ባለሙያዎችን ከአገልግሎት ፈላጊዎች ጋር የሚያገናኝ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ቀብር ማስፈጸም ስራ፣ የምግብ  ዝግጅት ስራዎችን፣ የእንስሳት ህክምና እንዲሁም ከ30 በላይ የአገልግሎት ሰጪ ባለሙያ ድርጅቶችንና ግለሰቦችን ከአገልግሎት ፈላጊዎች ጋር ይገናኛል ተብሏል።
ማንኛውም የአገልግሎቱ ፈላጊዎች በሞባይል መተግበሪያው አሊያም በ625 የስልክ መስመር ላይ በመደወል አገልግሎቱን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ጥራትና  አስተማማኝነት ያለው አገልግሎትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ዕድል የሚሰጥ ነው ተብሏል። አገልግሎቱ በተለያዩ ሙያዎች ሰልጥነው ከአገልግሎት ፈላጊዎች ጋር በቀላሉ ለመገናኘት እድል ላላገኙ ባለሙያዎች የሥራ ዕድል የሚከፍት መሆኑ ታውቋል።
የአገልግሎት ተጠቃሚው ከአገልግሎት አሰጣጡ ጋር በተያያዘ የሚያነሳቸው ቅሬታዎችን ለማስወገድ የሚቻልበት አሰራር ይዞ መምጣቱም ገልጿል።


Read 11596 times