Saturday, 18 June 2022 18:18

ታሪክ - ለልጆች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ቀበጧ ቡችላ

           በጥንት ጊዜ አንዲት ውሻ ከትናንሽ ልጆቿ (ቡችሎች) ጋር በአንድ የእርሻ አካባቢ ላይ ይኖሩ ነበር። በእርሻው አካባቢ የውሃ ጉድጓድም ነበር። እናቲቱ ውሻ ልጆችዋ ወደ ውሃ ጉድጓዱ አቅራቢያ እንዳይደርሱ ወይም በዚያ አካባቢ እንዳይጫወቱ ሳትነግራቸው የቀረችበት ጊዜ የለም፡፡ ሁሌም ትመክራቸው ታስጠነቅቃቸው ነበር፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን ከቡችሎቹ አንደኛዋ ቀበጥ ቡችላ በእናታቸው የተከለከሉትን የውሃ ጉድጓድ ለማየት ጥልቅ ጉጉት  አደረባት። የእናቷን ምክርና ማስጠንቀቂያ ችላ ብላ ወደ ጉድጓዱ  ለመሄድ ተነሳሳች፡፡
ቡችላዋ ብቻዋን ተደብቃ ወደ ውሃ ጉድጓዱ ሄደች። ወደ ጉድጓዱ ስትመለከትም በውሃው ውስጥ የራሷን ምስል ነጸብራቅ አየች፡፡ እሷ ግን በጉድጓዱ ውሃ ውስጥ ሌላ ውሻ ያለ ነበር የመሰላት።  ከዚያ  ውሻ ጋርም  ለጠብ ተጋበዘች፡፡
ቡችላዋ በጣም ከመናደዷ የተነሳም የውሃ ጉድጓዱ ውስጥ ዘልላ ገባች። እንዳሰበችው ግን ሌላ ውሻ አላገኘችም። ከዚያ ማን ያውጣት?! መጮህና ማልቀስ ጀመረች። ከብዙ ጩኸትና ለቅሶ በኋላ ገበሬው ደርሶ አወጣት፡፡ ከሞት አተረፋት። ከዚያ ጊዜ በኋላ ቡችላዋ ወደ ውሃ ጉድጓዱ ተመልሳ ሄዳ አታውቅም።
ውድ ልጆች፡- ከዚህ ታሪክ የምንማረው ቁም ነገር፤ የታላላቆችን ምክርና ትዕዛዝ መስማትና ማክበር ተገቢ መሆኑን ነው። ቡችላዋ የእናቷን ምክር ባለመስማቷ የገጠማትን አደጋ ከታሪኩ ተገንዝበናል፡፡

Read 1289 times