Saturday, 18 June 2022 19:54

“እግዜር ቅኔ አማረው” የግጥም ስብስብ መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በገጣሚዋና በህክምና ባለሙያዋ ዶ/ር አበባ የሺጥላ የተሰናዳውና 66 ያህል ግጥሞችን የያዘው “እግዜር ቅኔ አማረው” የተሰኘው የግጥም ስብስብ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
በመፅሐፉ ውስጥ የተካተቱ ግጥሞች በርካታ ማህበራዊ ርዕስ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ፍሬያማ ግጥሞች ስለመሆናቸው መፅሐፉን የማንበብ ዕድል የገጠማቸው ግለሰቦች ገልፀዋል፡፡ ዶ/ር አበባ የሺጥላ ከውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሀኪምነቷ ባሻገር እጅግ ጠንካራና በተለያዩ ማህራዊ ጉዳዮችም ንቁ ተሳትፎ ያላትና የተዋጣላት ገጣሚ እንደሆነችም ለማወቅ ተችሏል፡፡
“እግዜር ቅኔ አማረው” የግጥም ስብስብ መፅፍ በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን በ102 ገጽ ተቀንብቦ በ150 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 11909 times