Saturday, 18 June 2022 19:57

“ባለዋርካው ሰጉራ” የልጆች መፅሐፍ ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በዳራሲ ህሩይ ሮሜል የተጻፈው “ባለዋርካው ሰጉራ”  የተሰኘ የልጆች መፅሐፍ ባለፈው እሁድ ሰኔ 5 ቀን 2014 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በአክሱም ሆቴል ተመረቀ፡፡
መፅሐፉ በዋናነት መቼቱን ጅማ አድርጎ በማህበረሰቡ የሚነገሩ ተረቶችንና አፈታሪኮችን በማዘጋጀት ለልጆች በሚገባና በሚመች መልኩ ተደርጎ መሰናዳቱ ታውቋል፡፡ መፅሀፉን የፃፈው ደራሲ ህሩይ ሮሜል በህጻናትና በልጆች ላይ በስፋትና በጥልቀት የመስራት ህልም የነበረው ሲሆን ከነዚህ ህልሞቹ አንዱ የህጻናት መፅሐፍ መፃፍ በመሆኑ መፅሐፉን ፅፎ ጨርሶ የህትመት ብርሃን ሳያይ የደራሲው ህይወት ማለፉን መፅሐፉን አሳትመው ያስመረቁት የደራሲው ጓደኞች ተናግረዋል፡፡
የህሩይ ህልም እውን ለማድረግ ገንዘብ አዋጥተው ያሳተሙት ጓደኞቹ የእግዜር ድልድይ፣ ላምባ፣ የአርበኛው ልጅ በሚሉና በሌሎችም ስራዎቹ የምናውቀው የፊልም ባለሙያ አንተነህ ሀይሌን ጨምሮ ሌሎች ጓደኞቹ ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ መሆናቸው ታውቋል፡፡ “ባለዋርካው ሰጉራ” ሲመረቅ የመፅፍ ዳሳሳ፣ የደራሲው የህይወት ታሪክና ህልም በዕለቱ ለታዳሚ የቀረበ ሲሆን፣ መፅሐፉ ለዚህ እንደበቃ ለተረባረቡት ሁሉ የደራሲው ባለቤት ምስጋና አቅርባለች፡፡  መፅሀፉ በ66 ገፅ ተቀንብቦ በ230 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 11381 times