Friday, 08 July 2022 00:00

አሐዱ ባንክ በመጪው ቅዳሜ ሥራ ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


              በ564 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታልና በ702 ሚሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል፣ በ10ሺ ባለአክሲዮኖች የተደራጀው አሐዱ ባንክ፤ በመጪው ቅዳሜ ሐምሌ 9 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራ እንደሚጀምር አስታወቀ።
በአገልግሎት አሰጣጥና በቴክሎጂ አጠቃቀም በኩል ያለውን ሰፊ ክፍተት ለማጥበብ አቅዶ የተነሳው አሐዱ ባንክ፤ ይህንን የተሻለ የባንክ አደረጃጀት ይዞ ወደ ገበያ  የሚገባ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ነው ተብሏል።
የአሐዱ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤና የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ እሸቱ ፋንታዬ በማርዮት ሆቴል ከትላንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተመለከተው፤ ባንኩ በየዓመቱ ከሚያቀርበው ብድር እስከ 15 በመቶ የሚደርሰውን ለስራ ፈጣሪዎችና ለአነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያመቻች ይሆናል ። የባንኩን አገልግሎት በስፋት ለማዳረስ የዲጂታል አማራጮችን እንደሚጠቀምም ተገልጿል።
በአገራችን ከተለመደውና ከብዙሃን ሰብስቦ ለጥቂቶች የመስጠት የባንክ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መሆኑን ያስታወሱት የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተ አንተነህ ሰብስቤ፤ አሐዱ ባንክ በተቃራኒው ከብዙሃን ፋይናንስ ሰብስቦ ለብዙሃን የማያዳረስ ዕቅድ እንዳለው ተናግረዋል።
ባንኩ ቅርንጫፎቹን በስፋት በመክፈት አገልግሎቱን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀቱን የገለጹት የባንኩ የስራ ሃላፊዎች፤ በቀጣይም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመደገፍ በሞባይል አማካኝነት የባንክ ሂሳብን  በቀላሉ መክፈትና ማንቀሳቀስ የሚቻልበትን አሰራር ተግባራዊ ያደርጋል ብለዋል፡፡
ከሐምሌ 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በተለያዩ ማህበራዊ ኃላፊነቶችን ለመስጠት በሚያስችሉ ተግባራት ላይ አተኩሮ እንደሚቆይና “አንድ ቅርንጫፍ ለአንድ ልጅ” በሚል ባንኩ በሚከፍታቸው ቅርንጫፎች ቁጥር ልክ ድጋፍና እገዛ ለሚያስፈልጋቸው ልጆች ዓመታዊ ወጪያቸውን እንደሚሸፍን ገልጿል።
የአገር ቅርስና እስቶችን ተንከባክቦና ጠብቆ ለትውልድ ማስተላፍ የሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ሃላፊነት ነው ብሎ የሚያምነው ባንኩ የአገራችን ታላቅ ሃብትና ቅርስ ለሆነውን የቅዱስ ላሊበላ ገዳም ዕድሳት የ500 ሺ ብር ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቋል፡፡
ባንኩ በሚቀጥሉት ሁለት ወራት የቅርንጫፎቹን ቁጥር 50 እንደሚያደርስም ተገልጿል።


Read 1863 times