ዋልያ መጻሕፍት በየሳምንቱ የሚያዘጋጀው የመጻህፍት ውይይት መርሓግብር፣ በዛሬው ዕለት የዶ/ር በድሉ ዋቅጅራን “የ፭ ግጥም እድሜ” መጽሐፍ ለውይይት ያቀርባል፡፡
በዚህ መርሃግብር ታዳሚያን ከገጣሚው ጋር ከሚያደርጉት የፊት ለፊት ውይይት በተጨማሪ መጽሐፍ የማስፈረም ሥነሥርዓት እንደሚኖር ታውቋል፡፡
መርሐግብሩን ዛጎል የመጻሕፍት ባንክና ዋልያ መጻሕፍት በትብብር የሚያሰናዱት ሲሆን ዘወትር ቅዳሜ በመደበኛነት አራት ኪሎ፣ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ፣ኢክላስ ህንጻ ላይ ከ10 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡