Saturday, 24 September 2022 16:49

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል ዳታ ማዕከል ሥራውን ጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ሬድፎክስ ሶሉሽንስ ግሩፕ ያስገነባው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል ዳታ ማዕከል ሥራውን የጀመረ ሲሆን ተፈላጊ ለሆነው የአይሲቲ ማዕከል ዘመኑ የደረሰበትን መሠረተ ልማት ተደራሽነትን፣ብቃትንና ቀጣይነትን ይዞ መጥቷል ተብሏል፡፡
ሬድፎክስ ሞጁላር ዳታ ሴንተር 1 ተብሎ የሚጠራው የዳታ ማዕከል  በአዲስ አበባ በሚገኘው አይሲቲ ፓርክ ውስጥ ተገንብቶ ሥራውን ጀምሯል፡፡ የሬድፎክስ ሶሉሽን ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አዳነ ካሣዬ፤ “ግባችን በክፍለ አህጉራችን ቀዳሚው የዳታ ሴንተር አቅራቢ መሆን ነው” ብለዋል፡፡  
ዳታ ማዕከሉ በይፋ ሥራውን የጀመረበት ሥነሥርዓት  ሰኞ መስከረም 9 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሃያት ሬጀንሲ ሜትሮ የተከናወነ ሲሆን ታዋቂ ሰዎች በሁነቱ ላይ ታድመዋል፡፡ ሬድፎክስ በቴሌኮምና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የበርካታ ዓመታት ልምድና ከፍተኛ ዕውቀት ባላቸው እንዲሁም በተለያዩ የቢዝነስ ተቋማት በርካታ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥራዎችንና ፕሮጀክቶችን በመሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ባለሙያዎች የተቋቋመ ሲሆን ዓላማውም በተሟላ የዳታ ማዕከል ግንባታ የአገሪቱን አቅም ማሳደግ ነው ተብሏል፡፡

Read 1171 times